መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 31

31
1ይህም ሁሉ በተ​ፈ​ጸመ ጊዜ በይ​ሁዳ ከተ​ሞች የተ​ገኙ እስ​ራ​ኤል ሁሉ ወጥ​ተው ዐም​ዶ​ቹን ሰበሩ፤ ዐፀ​ዶ​ች​ንም ኮረ​ብ​ታ​ዎ​ች​ንም አፈ​ረሱ፤ መሠ​ዊ​ያ​ው​ንም አጠፉ። በይ​ሁ​ዳና በብ​ን​ያ​ምም ሁሉ ደግ​ሞም በኤ​ፍ​ሬ​ምና በም​ናሴ የነ​በ​ሩ​ትን ፈጽ​መው እስከ ዘለ​ዓ​ለሙ አጠ​ፉ​አ​ቸው። የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ሁሉ ወደ ርስ​ታ​ቸ​ውና ወደ ከተ​ሞ​ቻ​ቸው ተመ​ለሱ።
2ሕዝ​ቅ​ያ​ስም የካ​ህ​ና​ት​ንና የሌ​ዋ​ው​ያ​ንን ሰሞን በየ​ክ​ፍ​ላ​ቸ​ውና በየ​አ​ገ​ል​ግ​ሎ​ታ​ቸው፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አደ​ባ​ባይ በሮች የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የደ​ኅ​ን​ነ​ቱን መሥ​ዋ​ዕት ያቀ​ር​ቡና ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ፥ ያመ​ሰ​ግ​ኑም፥ ያከ​ብ​ሩም ዘንድ ካህ​ና​ቱ​ንና ሌዋ​ው​ያ​ኑን መደበ። 3በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕግ እንደ ተጻፈ በጥ​ዋ​ትና በማታ በሰ​ን​በ​ታ​ቱም፥ በመ​ባ​ቻ​ዎ​ቹም፥ በበ​ዓ​ላ​ትም ለሚ​ቀ​ር​በው ለሚ​ቃ​ጠ​ለው መሥ​ዋ​ዕት ንጉሡ ከገ​ን​ዘቡ የሚ​ከ​ፍ​ለ​ውን ወሰነ። 4በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ለአ​ገ​ል​ግ​ሎት እን​ዲ​ጸኑ ለካ​ህ​ና​ቱና ለሌ​ዋ​ው​ያን ድር​ሻ​ቸ​ውን ይሰጡ ዘንድ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖ​ሩ​ትን ሕዝብ አዘዘ። 5ይህ​ንም ነገር እን​ዳ​ዘዘ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የእ​ህ​ሉ​ንና የወ​ይ​ኑን፥ የዘ​ይ​ቱ​ንና የማ​ሩ​ንም፥ የእ​ር​ሻ​ው​ንም ፍሬ መጀ​መ​ሪያ ሁሉ ሰጡ፤ የሁ​ሉ​ንም ዐሥ​ራት አብ​ዝ​ተው አቀ​ረቡ። 6በይ​ሁ​ዳም ከተ​ሞች የሚ​ኖሩ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልና የይ​ሁዳ ልጆች የበ​ሬ​ዉ​ንና የበ​ጉን፥ የፍ​የ​ሉ​ንም ዐሥ​ራት አመጡ፤ ለአ​ም​ላ​ካ​ቸው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቀደ​ሱት፤ ከም​ረ​ውም አኖ​ሩት። 7በሦ​ስ​ተ​ኛ​ውም ወር መከ​መር ጀመሩ፤ በሰ​ባ​ተ​ኛ​ውም ወር ጨረሱ። 8ሕዝ​ቅ​ያ​ስና አለ​ቆ​ቹም መጥ​ተው ክም​ሩን ባዩ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገኑ። ሕዝ​ቡን እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ባረኩ። 9ሕዝ​ቅ​ያ​ስም ካህ​ና​ቱ​ንና ሌዋ​ው​ያ​ኑን ስለ ክምሩ ጠየቀ። 10ከሳ​ዶ​ቅም ወገን የሆነ ታላቁ ካህን ዓዛ​ር​ያስ፥ “ሕዝቡ መባ​ውን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ማቅ​ረብ ከጀ​መረ ወዲህ በል​ተ​ናል፤ ጠጥ​ተ​ና​ልም፤ ጠግ​በ​ና​ልም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሕዝ​ቡን ባር​ኮ​አ​ልና ብዙ ተር​ፎ​አል፤ ከዚ​ህም ገና ብዙ ተረፈ” ብሎ ተና​ገረ።
11ሕዝ​ቅ​ያ​ስም ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ጎተራ ያዘ​ጋጁ ዘንድ አዘዘ፤ እነ​ር​ሱም አዘ​ጋጁ። 12መባ​ኡ​ንና ዐሥ​ራ​ቱን፥ የተ​ቀ​ደ​ሱ​ት​ንም በእ​ም​ነት ወደ​ዚያ አገቡ። ሌዋ​ዊ​ውም ኮክ​ን​ያስ ተሾ​መ​ባ​ቸው፥ ወን​ድ​ሙም ሰሜኢ በማ​ዕ​ርግ ሁለ​ተኛ ነበረ፤ 13ንጉ​ሡም ሕዝ​ቅ​ያ​ስና የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አለቃ ዓዛ​ር​ያስ እንደ አዘዙ ኢዮ​ኤል፥ ዓዛ​ዝያ፥ አና​ኤት፥ ኡሳ​ሄል፥ ኢያ​ሪ​ሞት፥ ኢዮ​ዛ​ብድ፥ ኤል​ሄል፥ ሰማ​ኪያ፥ መሐት፥ በና​ያ​ስና ልጆቹ፥ ከኮ​ክ​ን​ያ​ስና ከወ​ን​ድሙ ከሰ​ሜኢ እጅ በታች ተቈ​ጣ​ጣ​ሪ​ዎች ነበሩ። 14የሌ​ዋ​ዊ​ውም የይ​ም​ላእ ልጅ የም​ሥ​ራቁ ደጅ በረኛ ቆሬ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መባና የተ​ቀ​ደ​ሱ​ትን ነገ​ሮች እን​ዲ​ያ​ካ​ፍል ሕዝቡ በፈ​ቃ​ዳ​ቸው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በአ​ቀ​ረ​ቡት ላይ ተሾመ። 15በካ​ህ​ና​ቱም ከተ​ሞች#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በካ​ህ​ናቱ እጅ” ይላል። ለታ​ላ​ላ​ቆ​ችና ለታ​ና​ና​ሾች ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው በየ​ሰ​ሞ​ና​ቸው ክፍ​ላ​ቸ​ውን በእ​ም​ነት ይሰጡ ዘንድ ኤዶም፥ ብን​ያስ፥ ኢያሱ፥ ሴሚ፥ አማ​ርያ፥ ኮክ​ን​ያስ ከእጁ በታች ነበሩ። 16ከሦ​ስ​ትም ዓመት ወደ ላይ ላሉ በየ​ሰ​ሞ​ና​ቸው ለሥ​ራ​ቸ​ውና ለአ​ገ​ል​ግ​ሎ​ታ​ቸው ዕለት ዕለት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ለሚ​ገቡ ወን​ዶች ሁሉ፥ 17በየ​አ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ቤት ለተ​ቈ​ጠሩ ካህ​ናት፥ ከሃያ ዓመ​ትም ወደ ላይ ላሉ በየ​ሥ​ር​ዐ​ታ​ቸ​ውና በየ​ሰ​ሞ​ና​ቸው ለተ​ቈ​ጠሩ ሌዋ​ው​ያን፥ 18በማ​ኅ​በ​ራ​ቸ​ውም ሁሉ በየ​ት​ው​ል​ዳ​ቸው ለተ​ቈ​ጠሩ ለሚ​ስ​ቶ​ቻ​ቸው፥ ለወ​ን​ዶ​ችና ለሴ​ቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ውም ይሰጡ ነበር፤ በእ​ም​ነት ፈጽ​መው ተቀ​ድ​ሰ​ዋ​ልና። 19ክህ​ነት ለሚ​ገ​ባ​ቸው ለአ​ሮን ልጆች ለካ​ህ​ናቱ፥ በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ዙሪያ ባሉ መሰ​ማ​ሪ​ያ​ዎ​ችና በሌ​ሎ​ችም ከተ​ሞች ላሉ ለወ​ን​ዶች ሁሉ፥ ከሌ​ዋ​ው​ያን ጋራ ለተ​ቈ​ጠሩ ሰዎ​ችም ሁሉ ከፍ​ለው ይሰጡ ዘንድ በስም የተ​ጠሩ ሰዎች ነበሩ።
20ሕዝ​ቅ​ያ​ስም በይ​ሁዳ ሁሉ እን​ዲህ አደ​ረገ፤ በአ​ም​ላ​ኩም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት መል​ካ​ም​ንና ቅን ነገ​ርን እው​ነ​ት​ንም አደ​ረገ። 21ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት አገ​ል​ግ​ሎት በጀ​መ​ረው ሥራ ሁሉ፥ በሕ​ጉና በት​እ​ዛ​ዙም አም​ላ​ኩን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በፍ​ጹም ልቡ ፈለ​ገው፤ ሥራ​ውም ሁሉ ተከ​ና​ወ​ነ​ለት።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ