መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 29

29
የይ​ሁዳ ንጉሥ የሕ​ዝ​ቅ​ያስ ዘመነ መን​ግ​ሥት
(2ነገ. 18፥1-3)
1ሕዝ​ቅ​ያ​ስም የሃያ አም​ስት ዓመት ጐል​ማሳ በነ​በረ ጊዜ መን​ገሥ ጀመረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ነገሠ፤ እና​ቱም የዘ​ካ​ር​ያስ ልጅ አብያ ትባል ነበር። 2አባ​ቱም ዳዊት እን​ዳ​ደ​ረገ ሁሉ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ቅን ነገ​ርን አደ​ረገ።
የቤተ መቅ​ደስ መን​ጻት
3በመ​ን​ግ​ሥ​ቱም በጸና ጊዜ#ዕብ. “በነ​ገሠ በመ​ጀ​መ​ሪያ ዓመት” ይላል። በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ወር የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ደጆች ከፈተ፤ አደ​ሳ​ቸ​ውም። 4ካህ​ና​ቱ​ንና ሌዋ​ው​ያ​ኑ​ንም አስ​መጣ፤ በም​ሥ​ራቅ በኩል ባለው አደ​ባ​ባ​ይም ሰበ​ሰ​ባ​ቸው፤ 5እን​ዲ​ህም አላ​ቸው፥ “ሌዋ​ው​ያን ሆይ፥ ስሙኝ፤ ራሳ​ች​ሁን አንጹ፤ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ች​ሁ​ንም አም​ላክ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ቀድሱ፤ ርኩ​ስን ነገር ሁሉ ከመ​ቅ​ደሱ አስ​ወ​ግዱ። 6አባ​ቶ​ቻ​ችን ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ርቀ​ዋል፤ በአ​ም​ላ​ካ​ች​ንም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ አድ​ር​ገ​ዋል፤ እር​ሱ​ንም ረስ​ተ​ዋል፤ ፊታ​ቸ​ው​ንም ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት መል​ሰ​ዋል፤ ጀር​ባ​ቸ​ው​ንም አዙ​ረ​ዋል፤ 7ደግ​ሞም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ደጆች ዘግ​ተ​ዋል፤ መብ​ራ​ቶ​ቹ​ንም አጥ​ፍ​ተ​ዋል፤ በመ​ቅ​ደ​ሱም ውስጥ ለእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ አላ​ጠ​ኑም፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት አላ​ቀ​ረ​ቡም።
8“ስለ​ዚ​ህም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍጣ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላይ ሆነ፤ በዐ​ይ​ና​ች​ሁም እን​ደ​ም​ታዩ ለድ​ን​ጋ​ጤና ለመ​ደ​ነ​ቂያ፥ ለመ​ዘ​በ​ቻም አሳ​ልፎ ሰጣ​ቸው። 9እነ​ሆም፥ ስለ​ዚህ አባ​ቶ​ቻ​ችሁ በሰ​ይፍ ወደቁ፤ ወን​ዶ​ችና ሴቶች ልጆ​ቻ​ች​ሁም፥ ሚስ​ቶ​ቻ​ች​ሁም የእ​ነ​ርሱ ሀገር ወዳ​ል​ሆነ ተማ​ረኩ፤ እስከ ዛሬም በዚያ ይኖ​ራሉ።#“የእ​ነ​ርሱ ሀገር ወዳ​ል​ሆነ ተማ​ረኩ ፤ እስከ ዛሬም ድረስ በዚያ ይኖ​ራሉ” የሚ​ለው በዕብ. የለም። 10አሁ​ንም የቍ​ጣ​ውን መቅ​ሠ​ፍት ከእኛ እን​ዲ​መ​ልስ ከእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጋር ቃል ኪዳን አደ​ርግ ዘንድ በልቤ አስ​ቤ​አ​ለሁ። 11አሁ​ንም#ዕብ. “ልጆች ሆይ” ይላል። በፊቱ ትቆ​ሙና ታገ​ለ​ግ​ሉት ዘንድ፥ አገ​ል​ጋ​ዮ​ቹም ትሆኑ ዘንድ፥ ታጥ​ኑ​ለ​ትም ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መር​ጦ​አ​ች​ኋ​ልና ቸል አት​በሉ።”
12ሌዋ​ው​ያ​ኑም፥ ከቀ​ዓት ልጆች የአ​ሜ​ሳእ ልጅ መኤ​ትና የዓ​ዛ​ር​ያስ ልጅ ኢዮ​ሔል፥ ከሜ​ራ​ሪም ልጆች የአ​ብዲ ልጅ ቂስና የያ​ሃ​ሌ​ል​ኤል ልጅ ዓዛ​ር​ያስ፥ ከጌ​ድ​ሶ​ንም ልጆች የዛ​ማት ልጅ ዮአ​ክና የዮ​አክ ልጅ ኢዮ​አድ፤ 13ከኤ​ል​ሳ​ፋ​ንም ልጆች ሳም​ሪና ኢዮ​ሔል፥ ከአ​ሳ​ፍም ልጆች ዘካ​ር​ያ​ስና ማታ​ን​ያስ፤ 14ከኤ​ማ​ንም ልጆች ኢዮ​ሔ​ልና ሰሜኢ፥ ከኢ​ዱ​ቱ​ንም ልጆች ሰማ​ዕ​ያና ኡዝ​ሔል ተነሡ። 15ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሰብ​ስ​በው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል እንደ ንጉሡ ትእ​ዛዝ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ያነጹ ዘንድ ራሳ​ቸ​ውን አነጹ። 16ካህ​ና​ቱም ያነ​ጹት ዘንድ#“ያነ​ጹት ዘንድ” የሚ​ለው በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ወደ ውስጥ ገቡ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መቅ​ደስ ያገ​ኙ​ትን ርኩስ ነገር ሁሉ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አደ​ባ​ባይ አወ​ጡት። ሌዋ​ው​ያ​ንም ወስ​ደው ወደ ሜዳ ወደ ቄድ​ሮን ወንዝ ጣሉት። 17በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ወር በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ቀን ያነጹ ጀመር፤ በዚ​ያ​ውም ወር በስ​ም​ን​ተ​ኛው ቀን ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ወለል ደረሱ፤ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤት በስ​ም​ንት ቀን አነጹ፤ በመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ውም ወር በዐ​ሥራ ስድ​ስ​ተ​ኛው ቀን ፈጸሙ። 18ወደ ውስ​ጡም ወደ ንጉሡ ወደ ሕዝ​ቅ​ያስ ገብ​ተው፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ሁሉ፥ ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሆ​ነ​ውን መሠ​ዊ​ያና ዕቃ​ው​ንም ሁሉ፥ የኅ​ብ​ስተ ገጹ​ንም ገበ​ታና ዕቃ​ውን ሁሉ አን​ጽ​ተ​ናል፤ 19ንጉ​ሡም አካዝ ነግሦ ሳለ በመ​ተ​ላ​ለፉ ያረ​ከ​ሰ​ውን ዕቃ ሁሉ አዘ​ጋ​ጅ​ተ​ናል፤ ቀድ​ሰ​ና​ልም፤ እነ​ሆም፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ፊት ሆነ​ዋል” አሉት።
20ንጉ​ሡም ሕዝ​ቅ​ያስ ማልዶ ተነሣ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ቤት#ዕብ. እና ግሪክ አባ. ሊ. “የከ​ተ​ማ​ይ​ቱን” ይላል። አለ​ቆች ሰበ​ሰበ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ወጣ። 21ስለ መን​ግ​ሥ​ቱና ስለ መቅ​ደ​ሱም፥ ስለ ሕዝ​ቡም ስለ እስ​ራ​ኤል ለኀ​ጢ​አት መሥ​ዋ​ዕት ሰባት ወይ​ፈ​ኖች፥ ሰባ​ትም አውራ በጎች፥ ሰባ​ትም የበግ ጠቦ​ቶች፥ ሰባ​ትም አውራ ፍየ​ሎች አመጡ። የአ​ሮ​ን​ንም ልጆች ካህ​ና​ቱን፥ “ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ውጡ” አላ​ቸው። 22ወይ​ፈ​ኖ​ቹ​ንም አረዱ፤ ካህ​ና​ቱም ደሙን ተቀ​ብ​ለው በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ረጩት፤ አውራ በጎ​ቹ​ንም አረዱ፤ ደሙ​ንም በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ረጩት፤ ጠቦ​ቶ​ቹ​ንም አረዱ፤ ደሙ​ንም በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ ረጩት። 23የኀ​ጢ​አት መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሆ​ኑ​ት​ንም አውራ ፍየ​ሎች በን​ጉ​ሡና በጉ​ባ​ኤው ፊት አቀ​ረቡ፤ እጃ​ቸ​ው​ንም ጫኑ​ባ​ቸው፤ 24ካህ​ና​ቱም አረ​ዱ​አ​ቸው፤ ንጉ​ሡም የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕ​ትና የኀ​ጢ​አት መሥ​ዋ​ዕት ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ እን​ዲ​ደ​ረግ አዝዞ ነበ​ርና ለእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ማስ​ተ​ስ​ረያ ያደ​ርጉ ዘንድ ደማ​ቸ​ውን በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ አቀ​ረቡ።
25ይህ​ንም ትእ​ዛዝ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በነ​ቢ​ያቱ እጅ አዝ​ዞ​አ​ልና እንደ ዳዊ​ትና እንደ ንጉሡ ባለ ራእይ እንደ ጋድ፥ እንደ ነቢ​ዩም እንደ ናታን ትእ​ዛዝ፥ ጸና​ጽ​ልና በገና፥ መሰ​ን​ቆም አስ​ይዞ ሌዋ​ው​ያ​ንን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አቆመ። 26ሌዋ​ው​ያ​ንም የዳ​ዊ​ትን የዜማ ዕቃ ይዘው፥ ካህ​ና​ቱም መለ​ከ​ቱን ይዘው ቆመው ነበር። 27ሕዝ​ቅ​ያ​ስም፥ “የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት በመ​ሠ​ዊ​ያው ላይ አሳ​ርጉ” አለ፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ው​ንም መሥ​ዋ​ዕት ማሳ​ረግ በተ​ጀ​መረ ጊዜ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መዝ​ሙር ደግሞ ተጀ​መረ፤ መለ​ከ​ቱም ተነፋ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ የዳ​ዊት ዜማ ዕቃ ተመታ። 28የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውም መሥ​ዋ​ዕት እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ ጉባ​ኤው ሁሉ ይሰ​ግዱ ነበር፤ መዘ​ም​ራ​ኑም ይዘ​ምሩ ነበር፤ መለ​ከ​ተ​ኞ​ችም ይነፉ ነበር። 29ማቅ​ረ​ቡ​ንም በፈ​ጸሙ ጊዜ ንጉሡ፥ ከእ​ር​ሱም ጋር የነ​በሩ ሁሉ አጐ​ነ​በሱ፤ ሰገ​ዱም። 30ንጉሡ ሕዝ​ቅ​ያ​ስና አለ​ቆ​ቹም በዳ​ዊ​ትና በነ​ቢዩ በአ​ሳፍ ቃል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግኑ ዘንድ ሌዋ​ው​ያ​ንን አዘዙ። በደ​ስ​ታም አመ​ሰ​ገኑ፤ አጐ​ነ​በ​ሱም፤ ሰገ​ዱም።
31ሕዝ​ቅ​ያ​ስም፥ “አሁን እጃ​ች​ሁን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ጽ​ታ​ችሁ ቅረቡ፤ መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንና የም​ስ​ጋ​ና​ውን መሥ​ዋ​ዕት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አምጡ” ብሎ ተና​ገረ። ጉባ​ኤ​ውም መሥ​ዋ​ዕ​ቱ​ንና የም​ስ​ጋ​ና​ውን መሥ​ዋ​ዕት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አመጡ፤ ልባ​ቸ​ውም የፈ​ቀደ ሁሉ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት አመጡ። 32ጉባ​ኤ​ውም ያመ​ጡት የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት ቍጥር ሰባ ወይ​ፈን፥ መቶም አውራ በጎች፥ ሁለት መቶም የበግ ጠቦ​ቶች ነበረ፤ ይህ ሁሉ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት ነበረ። 33የተ​ቀ​ደ​ሱ​ትም ቍጥር ስድ​ስት መቶ በሬ​ዎች፥ ሦስት ሺህም በጎች ነበረ። 34ነገር ግን ካህ​ናቱ ጥቂ​ቶች ነበ​ሩና የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ለመ​ግ​ፈፍ አይ​ች​ሉም ነበር፤ ስለ​ዚ​ህም ሌዋ​ው​ያን በቅን ልብ ከካ​ህ​ናት ይልቅ ይቀ​ደሱ ነበ​ርና ሥራው እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ፥ ካህ​ና​ቱም እስ​ኪ​ቀ​ደሱ ድረስ ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ሌዋ​ው​ያን ያግ​ዙ​አ​ቸው ነበር። 35የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውም መሥ​ዋ​ዕት ከደ​ኅ​ን​ነቱ መሥ​ዋ​ዕት ስብና ለሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውም መሥ​ዋ​ዕት ከሚ​ቀ​ር​በው የመ​ጠጥ ቍር​ባን ጋር ብዙ ነበረ። እን​ዲ​ሁም የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት አገ​ል​ግ​ሎት ተዘ​ጋጀ። 36ሕዝ​ቅ​ያ​ስና ሕዝ​ቡም ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለሕ​ዝቡ ስላ​ዘ​ጋ​ጀው ነገር ደስ አላ​ቸው። ይህ ነገር በድ​ን​ገት ተደ​ር​ጎ​አ​ልና።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ