መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልእ 17
17
የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሳፍጥ ዘመነ መንግሥት
1ከአሳም በኋላ ልጁ ኢዮሳፍጥ ነገሠ፤ ኢዮሳፍጥም በእስራኤል ላይ ጠነከረ። 2በተመሸጉትም በይሁዳ ከተሞች ሁሉ ሠራዊቱን አኖረ፤ በይሁዳም ሀገር፥ አባቱም አሳ በወሰዳቸው በኤፍሬም ከተሞች መሳፍንቱን አስቀመጠ። 3እግዚአብሔርም ከኢዮሳፍጥ ጋር ነበረ፤ በፊተኛዪቱም በአባቱ በዳዊት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በዳዊት” አይልም። መንገድ ሄዶአልና፥ ጣዖትንም አልፈለገምና፤ 4ነገር ግን የአባቱን አምላክ ፈለገ፤ በአባቱም ትእዛዝ ሄደ፤ በእስራኤልም ሥራ አይደለም። 5እግዚአብሔርም መንግሥቱን በእጁ አጸና፤ ይሁዳም ሁሉ እጅ መንሻ ለኢዮሳፍጥ አመጣ፤ እጅግም ብዙ ብልጥግናና ክብር ሆነለት። 6ልቡም በእግዚአብሔር መንገድ ከፍ ከፍ አለ፤ የኮረብታውን መስገጃዎችና የማምለኪያ አፀዱንም ከይሁዳ አስወገደ።
7በነገሠም በሦስተኛው ዓመት በይሁዳ ከተሞች ያስተምሩ ዘንድ መሳፍንቱንና ኀያላኑን ሰዎች አብድያስን፥ ዘካርያስን፥ ናትናኤልን፥ ሚኪያስን ላከ። 8ከእነርሱም ጋር ሌዋውያንን ሸማያን፥ ነታንያን፥ ዛባድያን፥ አሣሄልን፥ ሰሚራሞትን፥ ዮናታንን፥ አዶንያስን፥ ጦብያን፥ ጦባዶንያስን#“ጦባዶንያን” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ከእነርሱም ጋር ካህናቱን ኤሊሳማንና ኢዮራምን ላከ። 9እነርሱም የእግዚአብሔርን የሕጉን መጽሐፍ ይዘው በይሁዳ ያስተምሩ ነበር፤ ወደ ይሁዳም ከተሞች ሁሉ ተመላልሰው ሕዝቡን አስተማሩ።
10በይሁዳም ዙሪያ በነበሩ የምድር መንግሥታት ሁሉ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ድንጋጤ ሆነ፤ ከኢዮሳፍጥም ጋር አልተዋጉም። 11ከፍልስጥኤማውያንም ለኢዮሳፍጥ እጅ መንሻና የብር ግብር ያመጡ ነበር፤ ዐረባውያንም ደግሞ ከመንጎቻቸው ሰባት ሺህ ሰባት መቶ አውራ በጎችንና ሰባት ሺህ ሰባት መቶ አውራ ፍየሎችን#“ሰባት ሺህ ሰባት መቶ አውራ ፍየሎች” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። ያመጡለት ነበር። 12ኢዮሳፍጥም እየበረታና እጅግም እየከበረ ሄደ፤ በይሁዳም ግንቦችንና የተመሸጉ ከተሞችን#ዕብ. “የጎተራ ከተሞችን” ይላል። ሠራ። 13በይሁዳም ከተሞች ብዙ ሥራ ሠራ፤ በኢየሩሳሌምም ጽኑዓን ኀያላን ሰልፈኞች ነበሩት። 14ቍጥራቸውም እንደ አባቶቻቸው ቤት ይህ ነበረ፤ ከይሁዳ ሻለቆች አለቃው ዓድናስ፥ ከእርሱም ጋር ሦስት መቶ ሺህ ጽኑዓን ኀያላን ሰዎች ነበሩ፤ 15ከእርሱም በኋላ አለቃው ኢዮአናን፥ ከእርሱም ጋር ሁለት መቶ ሰማንያ ሺህ ሰዎች ነበሩ፤ 16ከእርሱም በኋላ እግዚአብሔርን የሚያገለግል የዝክሪ ልጅ ማስያስ፥ ከእርሱም ጋር ሁለት መቶ ሺህ ጽኑዓን ኀያላን ሰዎች ነበሩ። 17ከብንያምም ጽኑዕ ኀያል የነበረው ኤሊያዳ፥ ከእርሱም ጋር ቀስት የሚገትሩ፥ ወንጭፍ የሚወነጭፉ ሁለት መቶ ሺህ ሰዎች ነበሩ፤ 18ከእርሱም በኋላ ዮዛባድ፥ ከእርሱም ጋር ለሰልፍ የተዘጋጁ መቶ ሰማንያ ሺህ ሰዎች ነበሩ። 19ንጉሡ በተመሸጉ በይሁዳ ከተሞች ሁሉ ካኖራቸውም ሌላ እነዚህ ንጉሡን ያገለግሉ ነበር።
Currently Selected:
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልእ 17: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ