መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ቀዳ​ማዊ 16

16
1የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ታቦት ይዘው ገቡ፤ ዳዊ​ትም በተ​ከ​ለ​ላት ድን​ኳን ውስጥ አኖ​ሩ​አት፤ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የደ​ኅ​ን​ነ​ቱን መሥ​ዋ​ዕ​ትም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት አቀ​ረቡ። 2ዳዊ​ትም የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ትና የደ​ኅ​ን​ነ​ቱን መሥ​ዋ​ዕት ማቅ​ረብ በፈ​ጸመ ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስም ሕዝ​ቡን ባረከ። 3ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ለወ​ን​ዱም ለሴ​ቱም ለእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ አን​ዳ​ንድ እን​ጀራ፥ አን​ዳ​ን​ድም ቍራጭ ሥጋ፥#“አን​ዳ​ን​ድም ቍራጭ ሥጋ” የሚ​ለው በግ​ሪኩ የለም። አን​ዳ​ን​ድም የዘ​ቢብ ጥፍ​ጥፍ አካ​ፈለ።
4በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ታቦት ፊት ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ፥ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያወ​ድ​ሱት ዘንድ፥ ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ትና ያከ​ብ​ሩ​ትም ዘንድ ከሌ​ዋ​ው​ያን ወገን አቆመ። 5አለ​ቃ​ውም አሳፍ ነበረ፤ ከእ​ር​ሱም ቀጥሎ ዘካ​ር​ያስ፥ ኢያ​ሔል፥ ሰሜ​ራ​ሞት፥ ይሔ​ኤል፥ ማታ​ትያ፥ ኤል​ያብ፥ በና​ያስ፥ አብ​ዲ​ዶም፥ ይዒ​ኤል በመ​ሰ​ን​ቆና በበ​ገና፥ አሳ​ፍም በጸ​ና​ጽል ይዘ​ምሩ ነበር። 6ካህ​ና​ቱም በና​ያ​ስና የሕ​ዜ​ኤል በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቃል ኪዳን ታቦት ፊት ሁል​ጊዜ መለ​ከት ይነፉ ነበር።
7በዚ​ያም ቀን ዳዊት በአ​ሳ​ፍና በወ​ን​ድ​ሞቹ እጅ እግ​ዝ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዲ​ያ​መ​ሰ​ግኑ አስ​ቀ​ድሞ ትእ​ዛ​ዝን ሰጠ።
የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር
(መዝ. 104፥1-1595፥1-3105፥47-48)
8የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታቦት ፊት የዘ​መ​ር​ዋት መዝ​ሙር ይህች ናት፦
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግ​ኑት፤ ስሙ​ንም ጥሩ፤
ለአ​ሕ​ዛ​ብም ሥራ​ውን አውሩ።
9ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ተቀ​ኙ​ለት፥ ዘም​ሩ​ለት፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያደ​ረ​ገ​ውን ተአ​ም​ራ​ቱን ሁሉ ተና​ገሩ።
10በቅ​ዱስ ስሙ ክበሩ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈ​ልግ ልብ ደስ ይበ​ለው።
11እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ፈል​ጉት፥ ትጸ​ና​ላ​ች​ሁም፤
ሁል​ጊዜ ፊቱን ፈልጉ።
12የሠ​ራ​ትን ድንቅ አስቡ፥
ተአ​ም​ራ​ቱ​ንም፥ የአ​ፉ​ንም ፍርድ፤
13ባሪ​ያ​ዎቹ የእ​ስ​ራ​ኤል#ግእዙ “የአ​ብ​ር​ሃም” ይላል። ዘር፥
ለእ​ር​ሱም የተ​መ​ረ​ጣ​ችሁ የያ​ዕ​ቆብ ልጆች ሆይ፥
14እርሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችን ነው፤
ፍርዱ በም​ድር ሁሉ ነው።
15ቃል ኪዳ​ኑን ለዘ​ለ​ዓ​ለም፥
እስከ ሺህ ትው​ልድ ያዘ​ዘ​ውን ቃሉን አሰበ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አስቡ” ይላል።
16ለአ​ብ​ር​ሃም ያደ​ረ​ገ​ውን፥
ለይ​ስ​ሐ​ቅም የማ​ለ​ውን፤
17ለያ​ዕ​ቆብ ሥር​ዐት እን​ዲ​ሆን
ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም የዘ​ለ​ዓ​ለም ኪዳን እን​ዲ​ሆን አጸና፤
18እን​ዲ​ህም አለ፥ “ለአ​ንተ የከ​ነ​ዓ​ንን ምድር
የር​ስ​ታ​ች​ሁን ገመድ እሰ​ጣ​ለሁ፤”
19ይህም የሆ​ነው እነ​ርሱ በቍ​ጥር ጥቂ​ቶች ሰዎች፥
እጅግ ጥቂ​ቶ​ችና ስደ​ተ​ኞች ሲሆኑ ነው።
20ከሕ​ዝብ ወደ ሕዝብ፥
ከመ​ን​ግ​ሥ​ትም ወደ ሌላ ሕዝብ አለፉ።
21ሰው ግፍ ያደ​ር​ግ​ባ​ቸው ዘንድ አል​ፈ​ቀ​ደም፤
ስለ እነ​ር​ሱም ነገ​ሥ​ታ​ትን ገሠጸ።
22“የቀ​ባ​ኋ​ቸ​ውን አት​ንኩ፥
በነ​ቢ​ያ​ቴም ክፉ አታ​ድ​ርጉ” ብሎ፥
23ምድር ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ፤
ዕለት ዕለ​ትም ማዳ​ኑን አውሩ።
24ክብ​ሩን ለአ​ሕ​ዛብ፥
ተአ​ም​ራ​ቱ​ንም ለወ​ገ​ኖች ሁሉ ንገሩ።
25እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ታላቅ፥ ምስ​ጋ​ና​ውም ብዙ ነውና፤
በአ​ማ​ል​ክ​ትም ሁሉ ላይ የተ​ፈራ ነው።
26የአ​ሕ​ዛብ አማ​ል​ክት ሁሉ ጣዖ​ታት ናቸው፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ሰማ​ያ​ትን ሠራ።
27ክብ​ርና ግርማ በፊቱ፥
ኀይ​ልና ደስ​ታም በመ​ቅ​ደሱ ውስጥ ናቸው።
28እና​ንተ የአ​ሕ​ዛብ ወገ​ኖች ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አምጡ፥
ክብ​ር​ንና ኀይ​ልን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አምጡ።
29ለስሙ የሚ​ገባ ክብ​ርን ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አምጡ፤
ቍር​ባ​ንን ይዛ​ችሁ በአ​ደ​ባ​ባዩ ግቡ፤
በቅ​ድ​ስ​ና​ውም ስፍራ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስገዱ።
30ምድር ሁሉ በፊቱ ትነ​ዋ​ወ​ጣ​ለች፤
ዓለ​ም​ንም እን​ዳ​ት​ነ​ዋ​ወጥ አጸ​ናት።#ዕብ. “ዓለ​ሙም እን​ዳ​ይ​ና​ወጥ ጸን​ቶ​አል” ይላል።
31ሰማ​ያት ደስ ይበ​ላ​ቸው፥ ምድ​ርም ሐሤ​ትን ታድ​ርግ፤
በአ​ሕ​ዛብ መካ​ከል፥ “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነገሠ” በሉ።
32ባሕር በሞ​ላዋ ትና​ወ​ጣ​ለች፤
በረሃ በእ​ር​ስ​ዋም ያሉ ሁሉ ሐሤ​ትን ያድ​ርጉ።
33በም​ድር ሊፈ​ርድ ይመ​ጣ​ልና፥
የዱር ዛፎች በዚ​ያን ጊዜ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ደስ ይላ​ቸ​ዋል።
34እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ስ​ግኑ።
ቸር ነውና፥ ምሕ​ረ​ቱም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና።
35የመ​ዳ​ና​ችን አም​ላክ ሆይ፥ አድ​ነን፤
ቅዱስ ስም​ህን እና​መ​ሰ​ግን ዘንድ፥
በም​ስ​ጋ​ና​ህም እን​መካ ዘንድ፥
ከአ​ሕ​ዛብ ሰብ​ስ​በህ ታደ​ገን በሉ።
36ከዘ​ለ​ዓ​ለም እስከ ዘለ​ዓ​ለም፥
የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይባ​ረክ። ሕዝቡ ሁሉ አሜን ይበሉ፤
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ያመ​ስ​ግኑ።
ሥር​ዐተ አም​ልኮ
37እን​ዲ​ሁም በየ​ቀኑ እን​ደ​ሚ​ገ​ባ​ቸው በታ​ቦቱ ፊት ዘወ​ትር ያገ​ለ​ግሉ ዘንድ አሳ​ፍ​ንና ወን​ድ​ሞ​ቹን ተዋ​ቸው። 38አብ​ዲ​ዶ​ም​ንም፥ ስድሳ ስም​ን​ቱ​ንም ወን​ድ​ሞ​ቻ​ቸ​ውን፤ የኤ​ዶ​ታ​ምም ልጅ አብ​ዲ​ዶ​ምና ሖሳ በረ​ኞች ይሆኑ ዘንድ ተዋ​ቸው፤ 39ካህ​ኑን ሳዶ​ቅ​ንና ካህ​ና​ቱን ወን​ድ​ሞ​ቹን በገ​ባ​ዖን በኮ​ረ​ብ​ታው መስ​ገጃ ባለው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማደ​ሪያ ፊት አቆ​ማ​ቸው፥ 40ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ይነ​ግ​ራ​ቸው ዘንድ አገ​ል​ጋዩ ሙሴን እንደ አዘ​ዘው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሕግ እንደ ተጻፈ ሁሉ ለሚ​ቃ​ጠ​ለው መሥ​ዋ​ዕት በሚ​ሆ​ነው መሠ​ዊያ ላይ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት ሁል​ጊዜ ጥዋ​ትና ማታ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያቀ​ርቡ ዘንድ። 41ምሕ​ረ​ቱም ለዘ​ለ​ዓ​ለም ነውና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ያመ​ሰ​ግኑ ዘንድ ኤማ​ን​ንና ኤዶ​ታ​ምን፥ በስ​ማ​ቸው የተ​ጻ​ፉ​ትን ተመ​ር​ጠው የቀ​ሩ​ትን ከእ​ነ​ርሱ ጋር አቆመ። 42ከእ​ነ​ር​ሱም ጋር ካህ​ናቱ ከፍ አድ​ር​ገው ለማ​ሰ​ማት መለ​ከ​ትና ጸና​ጽል ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መዝ​ሙ​ራት የዜማ ዕቃ ይዘው ነበር፤ የኤ​ዶ​ታም ልጆች ግን በረ​ኞች ነበሩ። 43ሕዝቡ ሁሉ እያ​ን​ዳ​ንዱ ወደ ቤቱ ሄደ፤ ዳዊ​ትም ቤቱን ይባ​ርክ ዘንድ ተመ​ለሰ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ