መዝሙረ ዳዊት 124
124
1የዳዊት የዕርገት መዝሙር።
#
መዝ. 129፥1። ጌታ ከእኛ ጋር ባይሆን
እስራኤል እንዲህ ይበል፦
2ጌታ ከእኛ ጋር ባይሆን
ሰዎች በእኛ ላይ በተነሡ ጊዜ፥
3 #
ምሳ. 1፥12። ቁጣቸው በላያችን በነደደ ጊዜ፥
በዚያን ጊዜ ሕያዋን ሳለን በዋጡን ነበር፥
4 #
መዝ. 18፥5፤ 69፥2። በዚያን ጊዜ ውኃ ባሰጠመን ነበር፥
በነፍሳችንም ላይ ወራጅ ውኃ ባለፈ ነበር፥
5በዚያን ጊዜ የጐርፍ ውኃ በነፍሳችን ላይ ባለፈ ነበር።
6ለጥርሳቸው ንክሻ ያላደረገን ጌታ ይመስገን።
7ነፍሳችን እንደ ወፍ ከአዳኞች ወጥመድ አመለጠች፥
ወጥመድ ተሰበረ እኛም አመለጥን።
8 #
መዝ. 121፥2፤ 146፥6። ረድኤታችን ሰማይንና ምድርን በሠራ
በጌታ ስም ነው።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 124: መቅካእኤ
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ
![None](/_next/image?url=https%3A%2F%2Fimageproxy.youversionapi.com%2F58%2Fhttps%3A%2F%2Fweb-assets.youversion.com%2Fapp-icons%2Fam.png&w=128&q=75)
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ