መጽሐፈ መዝሙር 134
134
እግዚአብሔርን አመስግኑ
1እናንተ አገልጋዮቹ!
በሌሊት በመቅደሱ የምታገለግሉት ሁሉ፥
ኑ እግዚአብሔርን አመስግኑ!
2በመቅደሱ እጆቻችሁን ለጸሎት ዘርግታችሁ
እግዚአብሔርን አመስግኑ!
3ሰማይንና ምድርን የፈጠረ እግዚአብሔር
ከጽዮን ይባርካችሁ!
Currently Selected:
መጽሐፈ መዝሙር 134: አማ05
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997