መጽሐፈ ምሳሌ 3:27-32

መጽሐፈ ምሳሌ 3:27-32 አማ05

ርዳታ እንድታደርግለት ለሚገባው ሰው ዐቅምህ በሚፈቅድልህ መጠን በጎ ነገር ከማድረግ አትቈጠብ። የተቸገረ ጐረቤትህን ዛሬውኑ መርዳት ሲቻልህ “እሺ ነገ” እያልክ አታመላልሰው። አንተን ተማምኖ በአጠገብህ በሚኖረው ጐረቤትህ ላይ በተንኰል ክፉ ነገር ለማድረግ አታስብ። ምንም በደል ያላደረሰብህን ሰው ያለ ምክንያት አትክሰሰው። በግፈኞች ሰዎች አትቅና፤ ክፉ ሥራቸውንም አትከተል። እግዚአብሔር ክፉ አድራጊዎችን ይጠላል፤ ልበ ቅኖችን ግን አጥብቆ ይወዳቸዋል።