የYouVersion አርማ
የፍለጋ አዶ

መዝሙር 43

43
መዝሙር 43#43 በብዙ የዕብራይስጥ ቅጆች መዝሙር 42 እና 43 አንድ መዝሙር ነው።
በስደት ላይ ያለ ሌዋዊ ልቅሶ
1አምላክ ሆይ፤ ፍረድልኝ፤
ከጽድቅ ከራቀ ሕዝብ ጋር ተሟገትልኝ፤
ከአታላዮችና ከክፉዎች ሰዎችም አድነኝ።
2አምላክ ሆይ፤ አንተ ብርታቴ ነህና፣
ለምን ተውኸኝ?
ጠላትስ እያስጨነቀኝ፣
ለምን በሐዘን እመላለሳለሁ?
3ብርሃንህንና እውነትህን ላክ፤
እነርሱ ይምሩኝ፤
ወደ ተቀደሰው ተራራህ፣
ወደ ማደሪያህ ያድርሱኝ።
4እኔም ወደ እግዚአብሔር መሠዊያ አቀናለሁ፤
ፍጹም ደስታዬ ወደ ሆነው አምላክ እሄዳለሁ፤
እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፣
በበገና አመሰግንሃለሁ።
5ነፍሴ ሆይ፤ ለምን ትተክዢያለሽ?
ለምንስ በውስጤ ትታወኪያለሽ?
ተስፋሽን በአምላክ ላይ አድርጊ፤
አዳኜና አምላኬን፣
ገና አመሰግነዋለሁና።

Currently Selected:

መዝሙር 43: NASV

ማድመቅ

Share

Copy

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ