መዝሙር 28
28
መዝሙር 28
ልመናና ምስጋና
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጣራለሁ፤
ዐለቴ ሆይ፤ ሰምተህ እንዳልሰማ አትሁንብኝ፤
አንተ ዝም ካልኸኝ፤
ወደ ጕድጓድ እንደሚወርዱ እሆናለሁ።
2ለርዳታ በጮኽሁ ጊዜ፣
ወደ ቅዱስ ማደሪያህ፣
እጆቼን በዘረጋሁ ጊዜ፣
የልመናዬን ቃል ስማ።
3በልባቸው ተንኰል እያለ፣
ከባልንጀሮቻቸው ጋር በሰላም ከሚናገሩ፣
ከክፉ አድራጊዎችና
ከዐመፃ ሰዎች ጋር ጐትተህ አትውሰደኝ።
4እንደ ሥራቸው፣
እንደ ክፉ ተግባራቸው ክፈላቸው፤
እንደ እጃቸው ሥራ ስጣቸው፤
አጸፋውን መልስላቸው።
5 ለእግዚአብሔር ሥራ ግድ ስለሌላቸው፣
ለእጆቹም ተግባራት ስፍራ ስላልሰጡ፣
እርሱ ያፈርሳቸዋል፤
መልሶም አይገነባቸውም።
6የልመናዬን ቃል ሰምቷልና፣
እግዚአብሔር የተባረከ ይሁን።
7 እግዚአብሔር ብርታቴና ጋሻዬ ነው፤
ልቤ በእርሱ ይታመናል፤ እርሱም ዐግዞኛል፤
ልቤ ሐሤት አደረገ፤
በዝማሬም አመሰግነዋለሁ።
8 እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታታቸው ነው፤
ለቀባውም የመዳን ዐምባ ነው።
9ሕዝብህን አድን፤ ርስትህንም ባርክ፤
እረኛ ሁናቸው፤ ለዘላለሙም ዐቅፈህ ያዛቸው።
Currently Selected:
መዝሙር 28: NASV
ማድመቅ
Share
Copy
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.