መዝሙር 26
26
መዝሙር 26
የንጹሕ ሰው ጸሎት
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ሆይ፤ ያለ ነቀፋ እንደ መሆኔ፣
አንተው ፍረድልኝ።
ወዲያ ወዲህ ሳልልም፣
በእግዚአብሔር ታምኛለሁ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈትነኝ፤
መርምረኝም፤
ልቤንና ውስጤን መርምር፤
3ምሕረትህ ከፊቴ አልተለየምና፣
በእውነትህም ተመላለስሁ።
4ከማይረቡ ጋር አልተቀመጥሁም፤
ከግብዞችም ጋር አልተባበርሁም።
5የክፉዎችን ማኅበር ተጸየፍሁ፤
ከዐመፀኞችም ጋር አልቀመጥም።
6እጆቼን በየዋህነት እታጠባለሁ፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ መሠዊያህንም እዞራለሁ፤
7የምስጋናን ድምፅ አሰማ ዘንድ፣
ታምራትህንም አወራ ዘንድ ነው።
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ የምትኖርበትን ቤት፣
የክብርህን ማደሪያ ቦታ ወደድሁ።
9ነፍሴን ከኀጢአተኞች ጋር፣
ሕይወቴንም ከደም አፍሳሾች ጋር አታስወግዳት።
10በእነርሱ እጅ የተንኰል ዕቅድ አለ፤
ቀኝ እጃቸውም ጕቦን ያጋብሳል።
11እኔ ግን በተአማኒ ሕይወት እጓዛለሁ፤
አድነኝ፤ ምሕረትንም አድርግልኝ።
12እግሮቼ በደልዳላ ስፍራ ቆመዋል፤
በታላቅ ጉባኤ መካከልም እግዚአብሔርን እባርከዋለሁ።
Currently Selected:
መዝሙር 26: NASV
ማድመቅ
Share
Copy
ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.