1
ኦሪት ዘፍጥረት 3:6
መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)
ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፤ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፤ ለጥበብም መልካም እንድ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስው ጋር በላ።
Karşılaştır
ኦሪት ዘፍጥረት 3:6 keşfedin
2
ኦሪት ዘፍጥረት 3:1
እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኵለኚ ነበረ። ሴቲቱንም፤ በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአል? አላት።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:1 keşfedin
3
ኦሪት ዘፍጥረት 3:15
በአንተና በሴቲቱ መካከል፤ በዘርህና በዘርዋም መካከል ጠላትነትን አደርጋለሁ፤ እርሱ ራስህን ይቀጠቅጣል አንተም ሰኮናውን ትቀጠቅጣለህ።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:15 keşfedin
4
ኦሪት ዘፍጥረት 3:16
ለሴቲቱም አለ፤ በፀነሰሽ ጊዜ ጭንቅሽን እጅግ አበዛለሁ፤ በጭንቅ ትወልጃለሽ ፈቃድሽም ወደ ባልሽ ይሆናል፤ እርሱም ገዥሽ ይሆናል።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:16 keşfedin
5
ኦሪት ዘፍጥረት 3:19
ወደ ወጣህብት መሬት እስክትመለስ ድረስ በፊትህ ወዝ እንጀርን ትበላለህ፤ አፈር ነህና ወደ አፈርም ትመለሳለህና።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:19 keşfedin
6
ኦሪት ዘፍጥረት 3:17
አዳምም አለው፤ የሚስትህን ቃል ሰምተሃልና፤ ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍም በልተሃልና ምድር ከአንተ የተነሣ የተረገመች ትሁን፤
ኦሪት ዘፍጥረት 3:17 keşfedin
7
ኦሪት ዘፍጥረት 3:11
እግዚእብሔርም አለው፤ ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገርህ? ከእርሱ እንዳትበላ ካዘዝሁህ ዛፍ በውኑ በላህን?
ኦሪት ዘፍጥረት 3:11 keşfedin
8
ኦሪት ዘፍጥረት 3:24
አዳምንም አስወጣው፤ ወደ ሕይወት ዛፍ የሚወስደውንም መንገድ ለመጠበቅ ኪሩቤልንና የምትገለባበጥ የነበልበል ሰይፍን በዔድን ገነት ምሥራቅ አስቀመጠ።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:24 keşfedin
9
ኦሪት ዘፍጥረት 3:20
አዳምም ለሚስቱ ሔዋን ብሎ ስም አወጣ፤ የሕያዋን ሁሉ እናት ናትና።
ኦሪት ዘፍጥረት 3:20 keşfedin
Ana Sayfa
Kutsal Kitap
Okuma Planları
Videolar