ኦሪት ዘፍ​ጥ​ረት 5

5
የአ​ዳም ትው​ልድ
(1ዜ.መ. 1፥1-4)
1የሰ​ዎች የት​ው​ልድ መጽ​ሐፍ ይህ ነው። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አዳ​ምን በፈ​ጠረ ቀን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምሳሌ አደ​ረ​ገው፤ 2ወን​ድና ሴት አድ​ርጎ ፈጠ​ራ​ቸው፤ ባረ​ካ​ቸ​ውም። እነ​ር​ሱ​ንም በፈ​ጠ​ረ​በት ቀን ስሙን አዳም ብሎ ጠራው። 3አዳ​ምም ሁለት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ልጅ​ንም እንደ ምሳ​ሌው እንደ መልኩ ወለደ፤ ስሙ​ንም ሴት ብሎ ጠራው። 4አዳ​ምም ሴትን ከወ​ለደ በኋላ የኖ​ረው ሰባት መቶ ዓመት ሆነ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 5አዳ​ምም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
6ሴትም ሁለት መቶ አም​ስት ዓመት ኖረ፤ ሄኖ​ስ​ንም ወለደ፤ 7ሴትም ሄኖ​ስን ከወ​ለደ በኋላ ሰባት መቶ ሰባት ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 8ሴትም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ዐሥራ ሁለት ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
9ሄኖ​ስም መቶ ዘጠና ዓመት ኖረ፤ ቃይ​ና​ን​ንም ወለደ፤ 10ሄኖ​ስም ቃይ​ና​ንን ከወ​ለደ በኋላ ሰባት መቶ ዐሥራ አም​ስት ዓመት ኖረ። ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 11ሄኖ​ስም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ አም​ስት ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
12ቃይ​ና​ንም መቶ ሰባ ዓመት ኖረ፤ መላ​ል​ኤ​ል​ንም ወለደ፤ 13ቃይ​ና​ንም መላ​ል​ኤ​ልን ከወ​ለደ በኋላ ሰባት መቶ አርባ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 14ቃይ​ና​ንም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ዐሥር ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
15መላ​ል​ኤ​ልም መቶ ስድሳ አም​ስት ዓመት ኖረ፤ ያሬ​ድ​ንም ወለደ፤ 16መላ​ል​ኤ​ልም ያሬ​ድን ከወ​ለደ በኋላ ሰባት መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 17መላ​ል​ኤ​ልም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ስም​ንት መቶ ዘጠና አም​ስት ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
18ያሬ​ድም መቶ ስድሳ ሁለት ዓመት ኖረ፤ ሄኖ​ክ​ንም ወለደ፤ 19ያሬ​ድም ሄኖ​ክን ከወ​ለደ በኋላ ስም​ንት መቶ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 20ያሬ​ድም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ስድሳ ሁለት ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
21ሄኖ​ክም መቶ ስድሳ አም​ስት ዓመት ኖረ፤ ማቱ​ሳ​ላ​ንም ወለደ፤ 22ሄኖ​ክም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ አሰ​ኘው፤ ሄኖ​ክም ማቱ​ሳ​ላን ከወ​ለደ በኋላ ሁለት መቶ ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 23ሄኖ​ክም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ሦስት መቶ ስድሳ አም​ስት ዓመት ሆነ። 24ሄኖ​ክም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ደስ ስላ​ሰ​ኘው አል​ተ​ገ​ኘም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰው​ሮ​ታ​ልና።
25ማቱ​ሳ​ላም መቶ ሰማ​ንያ ሰባት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “መቶ ስድሳ ሰባት” ይላል። ዓመት ኖረ፤ ላሜ​ሕ​ንም ወለደ፤ 26ማቱ​ሳ​ላም ላሜ​ሕን ከወ​ለደ በኋላ ሰባት መቶ ሰማ​ንያ ሁለት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ስም​ንት መቶ ሁለት” ይላል። ዓመት ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም፥ ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 27ማቱ​ሳ​ላም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ዘጠኝ መቶ ስድሳ ዘጠኝ ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
28ላሜ​ሕም መቶ ሰማ​ንያ ሁለት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “መቶ ሰማ​ንያ ስም​ንት” ይላል። ዓመት ኖረ፤ ልጅ​ንም ወለደ። 29ስሙ​ንም ከሥ​ራዬ፥ ከእጄ ድካ​ምና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከረ​ገ​ማት ምድር ይህ ያሳ​ር​ፈኝ ዘንድ አለው ሲል “ኖኅ” ብሎ ጠራው። 30ላሜ​ሕም ኖኅን ከወ​ለደ በኋላ አም​ስት መቶ ስድሳ አም​ስት ዓመት#ዕብ. “አም​ስት መቶ ዘጠና አም​ስት” ይላል። ኖረ፤ ወን​ዶ​ች​ንም ሴቶ​ች​ንም ወለደ። 31ላሜ​ሕም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ሰባት መቶ አርባ ሰባት#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሰባት መቶ ሃምሳ ሦስት” ዕብ. “ሰባት መቶ ሰባ ሰባት” ይላል። ዓመት ሆነ፤ ሞተም።
32ለኖ​ኅም አም​ስት መቶ ዓመት ሆነው፤ ኖህም ሦስት ልጆ​ችን ወለደ፤ እነ​ር​ሱም ሴም፥ ካምና ያፌት ናቸው።

தற்சமயம் தேர்ந்தெடுக்கப்பட்டது:

ኦሪት ዘፍ​ጥ​ረት 5: አማ2000

சிறப்புக்கூறு

பகிர்

நகல்

None

உங்கள் எல்லா சாதனங்களிலும் உங்கள் சிறப்பம்சங்கள் சேமிக்கப்பட வேண்டுமா? பதிவு செய்யவும் அல்லது உள்நுழையவும்

உங்கள் அனுபவத்தைத் தனிப்பட்டதாக்க யூவெர்ஸன் குக்கீகளைப் பயன்படுத்துகிறது. எங்கள் வலைத்தளத்தைப் பயன்படுத்துவதன் மூலம், எங்கள் தனியுரிமைக் கொள்கையில் விவரிக்கப்பட்டுள்ளபடி குக்கீகளைப் பயன்படுத்துவதை நீங்கள் ஏற்கிறீர்கள்