1
ኦሪት ዘፍጥረት 32:28
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
ሰውየውም፦ “ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ ያዕቆብ አይባልም፤ ነገር ግን ከእግዚአብሔር ከሰውም ጋር ታግለህ አሸንፈሃልና እስራኤል ይባላል” አለው።
ஒப்பீடு
ኦሪት ዘፍጥረት 32:28 ஆராயுங்கள்
2
ኦሪት ዘፍጥረት 32:26
ከዚያ ሰውየው፦ “የንጋት ጎህ ሊቀድ ነውና ልቀቀኝ” አለው። እርሱም፦ “ካልባረክኸኝ አልለቅህም” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:26 ஆராயுங்கள்
3
ኦሪት ዘፍጥረት 32:24
ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ፥ አንድ ሰውም እስከ ንጋት ድረስ ሲታገለው አደረ።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:24 ஆராயுங்கள்
4
ኦሪት ዘፍጥረት 32:30
ስለዚህ ያዕቆብ፦ “እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሆኖም ሕይወቴ ተርፋለች” ሲል የዚያን ቦታ ስም “ጵኒኤል” ብሎ ጠራው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:30 ஆராயுங்கள்
5
ኦሪት ዘፍጥረት 32:25
ያ ሰው ያዕቆብን እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ፥ የጭኑን ሹልዳ ነካው፥ ያዕቆብም ሲታገለው የጭኑ ሹልዳ ከመገጣጠሚያው ላይ ተለያየ፤።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:25 ஆராயுங்கள்
6
ኦሪት ዘፍጥረት 32:27
ሰውየውም፦ “ስምህ ማን ነው?” አለው። እርሱም፦ “ያዕቆብ ነኝ” አለው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:27 ஆராயுங்கள்
7
ኦሪት ዘፍጥረት 32:29
ያዕቆብም፦ “ልለምንህ፥ ስምህን ንገረኝ” ብሎ ጠየቀው። እርሱም፦ “ስሜን ለምን ትጠይቃለህ?” አለው። በዚያም ስፍራ ባረከው።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:29 ஆராயுங்கள்
8
ኦሪት ዘፍጥረት 32:10
ለባርያህ ካሳየኸው ከጽኑ ፍቅርና ከታማኝነትህ ሁሉ ትንሽ ስንኳ የማይገባኝ ነኝ፥ በትሬን ብቻ ይዤ ይህን ዮርዳኖስን ተሻግሬ ነበር፥ አሁን ግን ለሁለት ወገን የተከፈልኩ ሆንሁ።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:10 ஆராயுங்கள்
9
ኦሪት ዘፍጥረት 32:32
ስለዚህም የያዕቆብን ጭን ይዞ የወርቹን ሹልዳ ነክቶታልና፥ የእስራኤል ልጆች እስከ ዛሬ ድረስ የወርችን (በጭን መጋጠሚያ ላይ ያለውን) ሹልዳ አይበሉም።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:32 ஆராயுங்கள்
10
ኦሪት ዘፍጥረት 32:9
ያዕቆብም አለ፦ “የአባቴ የአብርሃም አምላክ ሆይ፥ የአባቴም የይስሐቅ አምላክ ሆይ፥ ‘ወደ ትውልድ አገርህ ወደ ተወለድህበትም ስፍራ ተመለስ፥ በጎነትንም አደርግልሃለሁ’ ያልኸኝ ጌታ ሆይ፥
ኦሪት ዘፍጥረት 32:9 ஆராயுங்கள்
11
ኦሪት ዘፍጥረት 32:11
ከወንድሜ ከዔሳው እጅ አድነኝ፥ መጥቶ እንዳያጠፋኝ፥ እናቶችንም ከልጆች ጋር እንዳያጠፋ እኔ እፈራዋለሁና።
ኦሪት ዘፍጥረት 32:11 ஆராயுங்கள்
முகப்பு
வேதாகமம்
வாசிப்புத் திட்டங்கள்
காணொளிகள்