1
ሉቃስ 23:34
አዲሱ መደበኛ ትርጒም
ኢየሱስም፣ “አባት ሆይ፤ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው” አለ። እነርሱም ልብሱን በዕጣ ተከፋፈሉት።
Харьцуулах
ሉቃስ 23:34 г судлах
2
ሉቃስ 23:43
ኢየሱስም፣ “እውነት እልሃለሁ፤ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ” አለው።
ሉቃስ 23:43 г судлах
3
ሉቃስ 23:42
ደግሞም፣ “ኢየሱስ ሆይ፤ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ” አለው።
ሉቃስ 23:42 г судлах
4
ሉቃስ 23:46
ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ፣ “አባት ሆይ፤ መንፈሴን በእጅህ እሰጣለሁ” አለ፤ ይህንም ብሎ ሞተ።
ሉቃስ 23:46 г судлах
5
ሉቃስ 23:33
ቀራንዮ የተባለ ቦታ በደረሱ ጊዜ ሰቀሉት፤ ወንጀለኞቹንም አንዱን በቀኙ፣ ሌላውን በግራው ሰቀሏቸው።
ሉቃስ 23:33 г судлах
6
ሉቃስ 23:44-45
ጊዜው ስድስት ሰዓት ያህል ነበር፤ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስም በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ፤ የፀሓይ ብርሃን ተከልክሏልና። የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ተቀድዶ ለሁለት ተከፈለ።
ሉቃስ 23:44-45 г судлах
7
ሉቃስ 23:47
የመቶ አለቃውም የሆነውን ነገር ባየ ጊዜ፣ “ይህ ሰው በርግጥ ጻድቅ ነበር” ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።
ሉቃስ 23:47 г судлах
Нүүр хуудас
Библи
Тѳлѳвлѳгѳѳ
Видео