1
ኦሪት ዘፍጥረት 27:28-29
መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)
እግዚአብሔርም ከሰማይ ጠል ከምድርም የእህልንም የወይንንም ብዛት ይስጥህ አሕዛብ ይገዙልህ ሕዝብም ይስገዱልህ ለወንድሞችህ ጌት ሁን የእናትህም ልጆች ይስገዱልህ የሚረግምህ እርሱ ርጉም ይሁን የሚባርክህም ቡሩም ይሁን።
Bandingkan
Telusuri ኦሪት ዘፍጥረት 27:28-29
2
ኦሪት ዘፍጥረት 27:36
እርሱም አለ፦ በእውነት ስሙ ያዕቆብ ተባለ ሁለት ጊዜ አሰናክሎኛልና፤ ብኵርናዬን ወሰደ አሁንም እነሆ በረከቴን ወሰደ። ደግሞም፦ ለእኔ በረከትን አላስቀረህልኝምን? አለ።
Telusuri ኦሪት ዘፍጥረት 27:36
3
ኦሪት ዘፍጥረት 27:39-40
አባቱ ይስሐቅም መለሰ አለውም፦ እነሆ መኖሪያህ ከምድር ስብ ከላይ ከሚገኝ ከሰማይም ጠል ይሆናል፤ በሰይፍህም ትኖራለህ፥ ለወንድምህም ትገዛለህ ነገር ግን በተቃወምኸው ጊዜ ቀንበሩን ከአንገትህ ትጥላለይ።
Telusuri ኦሪት ዘፍጥረት 27:39-40
4
ኦሪት ዘፍጥረት 27:38
ዔሳውም አባቱን አለው፦ አባቴ ሆይ እኔንም ደግሞ ባርከኝ። ዔሳውም ቃሉን አንሥቶ አለቀሰ።
Telusuri ኦሪት ዘፍጥረት 27:38
Beranda
Alkitab
Rencana
Video