YouVersion Logo
Search Icon

የያዕቆብ መልእክት መግቢያ

መግቢያ
ይህ የያዕቆብ መልእክት ለዕለታዊ ኑሮ መመሪያ የሚሆኑ ሐሳቦችን ያዘለ ሲሆን የተጻፈውም በዓለም ሁሉ ለተበተኑ ዐሥራ ሁለት ነገዶች ነው፤ ጸሐፊው ጥበብን በተግባር ስለምናውልበት ዘዴ፥ ለክርስቲያናዊ አቀባበልና ጠባይ መመሪያ የሚሆኑ ነገሮችን ግልጥ በሆኑ ሥዕላዊ አነጋገሮች ያቀርባል፤ ስለ ድኽነትና ስለ ሀብት፥ ስለ ፈተና፥ ስለ መልካም ጠባይ፥ ስለ ቅናት፥ ስለ እምነትና በጎ ምግባር፥ ስለ አንደበት ጠቃሚነትና ጐጂነት፥ ስለ ጥበብ፥ እርስ በርስ ስለ መጣላት፥ ስለ ትዕቢትና ስለ ትሕትና፥ በሌሎች ላይ ስለ መፍረድ፥ ስለ ትምክሕት ስለ ትዕግሥትና ስለ ጸሎት፥ ክርስቲያኖች ሊያደርጉት ስለሚገባቸው ግዴታ በዝርዝር ጽፎአል።
መልእክቱ በክርስትና ሕይወት እምነት በተግባር ስለሚተረጐምበት ሁኔታ አጒልቶ ያሳያል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
መግቢያ 1፥1
እምነትና ጥበብ 1፥2-8
ድኽነትና ሀብት 1፥9-11
ፈተና 1፥12-18
የእግዚአብሔርን ቃል መስማትና ማድረግ 1፥19-27
አድልዎ እንዳይደረግ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ 2፥1-13
እምነትና ሥራ 2፥14-26
ክርስቲያንና አንደበቱ 3፥1-18
ክርስቲያንና ይህ ዓለም 4፥1—5፥6
ስለ ተለያዩ ነገሮች የተሰጠ ምክር 5፥7-20

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in