1
የማቴዎስ ወንጌል 27:46
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን ኢየሱስ፦ “ኤሎሄ! ኤሎሄ! ላማ ሰበቅታኒ?” ሲል በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም “አምላኬ! አምላኬ! ለምን ተውከኝ?” ማለት ነው።
Compare
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:46
2
የማቴዎስ ወንጌል 27:51-52
በዚያን ጊዜ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀዶ ከሁለት ተከፈለ፤ ምድርም ተናወጠች፤ አለቶችም ተሰነጠቁ፤ መቃብሮችም ተከፍተው ሞተው ከነበሩት ቅዱሳን ሰዎች ብዙዎች ከሞት ተነሡ።
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:51-52
3
የማቴዎስ ወንጌል 27:50
ኢየሱስ እንደገና በታላቅ ድምፅ ጮኸና ነፍሱን ሰጠ።
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:50
4
የማቴዎስ ወንጌል 27:54
የመቶ አለቃውና ከእርሱም ጋር ኢየሱስን ይጠብቁ የነበሩት የምድርን መናወጥና የሆነውንም ነገር ባዩ ጊዜ እጅግ ፈርተው “በእውነት ይህ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ!” አሉ።
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:54
5
የማቴዎስ ወንጌል 27:45
ከስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ጨለማ ሆነ።
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:45
6
የማቴዎስ ወንጌል 27:22-23
ጲላጦስም “ታዲያ፥ መሲሕ የተባለውን ኢየሱስን ምን ላድርገው?” አላቸው። ሁሉም “ይሰቀል!” ሲሉ መለሱ። ገዢውም ለምን? “እርሱ ያደረገው በደል ምንድን ነው?” አላቸው። እነርሱ ግን “ይሰቀል!” እያሉ አብዝተው ጮኹ።
Explore የማቴዎስ ወንጌል 27:22-23
Home
Bible
Plans
Videos