1
ምሳሌ 6:16-19
አዲሱ መደበኛ ትርጒም
እግዚአብሔር የሚጠላቸው ስድስት ነገሮች አሉ፤ የሚጸየፋቸውም ሰባት ናቸው፤ እነርሱም፦ ትዕቢተኛ ዐይን፣ ሐሰተኛ ምላስ፣ ንጹሕ ደም የሚያፈስሱ እጆች፣ ክፋትን የሚያውጠነጥን ልብ፣ ወደ ክፋት የሚቻኰሉ እግሮች፣ በውሸት ላይ ውሸት የሚጨምር ሐሰተኛ ምስክር፣ በወንድማማቾች መካከል ጠብን የሚጭር ሰው።
Compare
Explore ምሳሌ 6:16-19
2
ምሳሌ 6:6
አንተ ታካች፤ ወደ ጕንዳን ሂድ፤ ዘዴውን አስተውለህ ጠቢብ ሁን፤
Explore ምሳሌ 6:6
3
ምሳሌ 6:10-11
ጥቂት ማንቀላፋት፤ ጥቂት ማንጐላጀት፤ እጅን አጣጥፎ “እስቲ ጥቂት ልረፍ” ማለት፤ ድኽነት እንደ ወንበዴ፣ ዕጦትም መሣሪያ እንደ ታጠቀ ሰው ከተፍ ይልብሃል።
Explore ምሳሌ 6:10-11
4
ምሳሌ 6:20-21
ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ትእዛዝ አክብር፤ የእናትህንም ትምህርት አትተው። ምንጊዜም በልብህ አኑራቸው፤ በዐንገትህም ዙሪያ እሰራቸው።
Explore ምሳሌ 6:20-21
Home
Bible
Plans
Videos