መጽ​ሐፈ ሲራክ 5

5
የየ​ዕ​ለት የሕ​ይ​ወት መመ​ሪያ
1ገን​ዘ​ብ​ህን በከ​ንቱ አት​በ​ትን፤
በቃ​ኝም አት​በል።
2የሰ​ው​ነ​ት​ህን ፈቃድ አት​ከ​ተል።
3እኔ ኀይ​ለኛ ነኝ፤ ማንስ ይች​ለ​ኛል አት​በል፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቀ​ልን ይበ​ቀ​ላ​ልና።
4ኀጢ​አት ሠርቼ ፍዳ አል​ተ​ቀ​በ​ል​ሁም አት​በል፥
እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ብዙ ዘመን ይታ​ገ​ሣ​ልና።
5ስለ ኀጢ​አ​ትህ ንስሓ መግ​ባ​ትን አት​ፍራ።
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ምሕ​ረቱ ብዙ ነው
ኀጢ​አ​ቴ​ንም ይቅር ይለ​ኛል እያ​ልህ በኀ​ጢ​አት ላይ ኀጢ​አ​ትን አት​ጨ​ምር።
6ምሕ​ረ​ትም መቅ​ሠ​ፍ​ትም ከእ​ርሱ ዘንድ ይመ​ጣ​ልና፤
መቅ​ሠ​ፍ​ቱም በኀ​ጢ​አ​ተኛ ሰው ላይ ይወ​ር​ዳል።
7ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መገ​ዛ​ትን ቸል አት​በል።
ሞት ድን​ገት ትመ​ጣ​ለ​ችና ከቀን ቀን አታ​ሳ​ልፍ፤
ፍዳህ ከመ​ቅ​ሠ​ፍት ጋራ በመ​ጣ​ብህ ጊዜ በመ​ከራ ትጨ​ነ​ቃ​ለህ።
8በመ​ከ​ራህ ጊዜ አን​ተን ማዳን አይ​ች​ል​ምና፤
ለዐ​መፃ ገን​ዘብ አት​ሳሳ።
ራስን ስለ መግ​ዛ​ትና ግልጽ ስለ መሆን
9ለሰው ሁሉ ምሥ​ጢ​ር​ህን አታ​ውጣ።
የወ​ደ​ድ​ኸ​ው​ንም ሁሉ አት​ከ​ተል፤
ምላሱ ሁለት እንደ ሆነ ኀጢ​አ​ተኛ አት​ሁን።
10አን​ተስ በጥ​በ​ብህ ጸን​ተህ ኑር፤
ቃል​ህም አንድ ይሁን።
11ለመ​ስ​ማ​ትም ፈጣን ሁን፤
ቃልን ለመ​መ​ለስ ግን የዘ​ገ​የህ ሁን።
12የም​ት​ነ​ግ​ረው ካለህ ለባ​ል​ን​ጀ​ራህ ንገ​ረው፤
ያለ​ዚያ ግን እጅ​ህን ባፍህ ላይ አድ​ርግ።
13መከ​በ​ር​ህና መዋ​ረ​ድህ ከቃ​ልህ የተ​ነሣ ነው፤
የሰ​ውም ውድ​ቀቱ ከአ​ን​ደ​በቱ የተ​ነሣ ነው።
14ሐሜ​ተኛ አት​ሁን፥ በአ​ን​ደ​በ​ት​ህም አው​ታታ አት​ሁን፤
የሌባ እፍ​ረቱ ጥቂት ነው።
አን​ደ​በቱ ሁለት የሆነ ሰው ግን መከ​ራው ጽኑ ነው።
15በታ​ላ​ቁም በታ​ና​ሹም ሰው ዘንድ
ቸር ሆነህ ተገ​ለጥ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ