መዝ​ሙረ ዳዊት 73:1-12

መዝ​ሙረ ዳዊት 73:1-12 አማ2000

አቤቱ፥ ስለ ምን ለዘ​ወ​ትር ጣል​ኸን? በማ​ሰ​ማ​ሪ​ያህ በጎች ላይስ ቍጣ​ህን ለምን ተቈ​ጣህ? አስ​ቀ​ድ​መህ የፈ​ጠ​ር​ሃ​ትን ማኅ​በ​ር​ህን፥ የተ​ቤ​ዠ​ሃ​ት​ንም የር​ስ​ት​ህን በትር፥ በው​ስ​ጥዋ ያደ​ር​ህ​ባ​ትን የጽ​ዮ​ንን ተራራ ዐስብ። ጠላት በቅ​ዱ​ሳ​ንህ ላይ እንደ ከፋ መጠን፥ ሁል​ጊዜ በት​ዕ​ቢ​ታ​ቸው ላይ እጅ​ህን አንሣ። ጠላ​ቶ​ችህ በበ​ዓ​ልህ መካ​ከል ተመኩ፤ የማ​ያ​ው​ቁ​ት​ንም ምል​ክት ምል​ክ​ታ​ቸው አደ​ረጉ። እንደ ላይ​ኛው መን​ገድ፥ በዱር እን​ዳ​ሉም እን​ጨ​ቶች፥ በገ​ጀሞ በሮ​ች​ዋን ሰበሩ። እን​ዲሁ በመ​ጥ​ረ​ቢ​ያና በመ​ዶሻ ሰበ​ሩ​አት። መቅ​ደ​ስ​ህ​ንም በእ​ሳት አቃ​ጠሉ፤ የስ​ም​ህ​ንም ማደ​ሪያ በም​ድር ውስጥ አረ​ከሱ። አንድ ሆነው በል​ባ​ቸው በየ​ሕ​ዝ​ባ​ቸው አሉ፦ “ኑ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በዓ​ላት ከም​ድር እን​ሻር ምል​ክ​ቱ​ንም አና​ው​ቅም፥ ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ ነቢይ የለም፤ እኛም ከእ​ን​ግ​ዲህ ወዲህ አና​ው​ቅም።” አቤቱ፥ ጠላት እስከ መቼ ይሳ​ደ​ባል? ስም​ህ​ንስ ጠላት ሁል​ጊዜ ያስ​ቈ​ጣ​ዋል? አቤቱ፥ እጅ​ህን ፈጽ​መህ ለምን ትመ​ል​ሳ​ለህ? ቀኝ​ህ​ንም በብ​ብ​ትህ መካ​ከል፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ግን ከዓ​ለም አስ​ቀ​ድሞ ንጉሥ ነው፥ በም​ድ​ርም መካ​ከል መድ​ኀ​ኒ​ትን አደ​ረገ።