ኦሪት ዘሌ​ዋ​ው​ያን 24:1-9

ኦሪት ዘሌ​ዋ​ው​ያን 24:1-9 አማ2000

እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሙሴን እን​ዲህ ብሎ ተና​ገ​ረው፦ “መብ​ራ​ቱን ሁል ጊዜ እን​ድ​ታ​በ​ራ​በት ለመ​ብ​ራት ጥሩ ተወ​ቅጦ የተ​ጠ​ለለ የወ​ይራ ዘይት ያመ​ጡ​ልህ ዘንድ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች እዘ​ዛ​ቸው። በም​ስ​ክሩ ድን​ኳን ከመ​ጋ​ረ​ጃው ውጭ አሮ​ንና ልጆቹ ከማታ እስከ ማለዳ ድረስ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ሁል ጊዜ ያበ​ሩ​ታል፤ ለዘ​ለ​ዓ​ለም ለልጅ ልጃ​ችሁ ሥር​ዐት ይሁን። በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በጥሩ መቅ​ረዝ ላይ መብ​ራ​ቶ​ቹን ሁል ጊዜ እስ​ኪ​ነጋ አብ​ሩ​አ​ቸው። “የስ​ንዴ ዱቄት ወስ​ደህ ዐሥራ ሁለት ኅብ​ስት ጋግር፤ በእ​ያ​ን​ዳ​ንዱ ኅብ​ስት ውስጥ ከመ​ስ​ፈ​ሪ​ያው ከዐ​ሥር እጅ ሁለት እጅ ይሁን። እነ​ዚ​ህ​ንም ስድ​ስት ስድ​ስ​ቱን በሁ​ለት ተርታ አድ​ር​ገህ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት በን​ጹሕ ገበታ ላይ አኑ​ራ​ቸው። በሁ​ለ​ቱም ተራ ንጹሕ ዕጣ​ንና ጨው ታደ​ር​ጋ​ለህ፤ እነ​ዚ​ህም ነገ​ሮች በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ለመ​ታ​ሰ​ቢያ ለተ​ዘ​ጋ​ጁት ኅብ​ስ​ቶች ይሁኑ። በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ሁል ጊዜ በሰ​ን​በት ቀን ሁሉ ያድ​ር​ጉት፤ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ዘንድ የዘ​ለ​ዓ​ለም ቃል ኪዳን ነው። ለአ​ሮ​ንና ለል​ጆ​ቹም ይሁን፤ በእ​ሳት ከተ​ደ​ረ​ገው ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቍር​ባን ለዘ​ለ​ዓ​ለም ሥር​ዐት ለእ​ርሱ ቅዱሰ ቅዱ​ሳን ነውና በተ​ቀ​ደሰ ስፍራ ይብ​ሉት።”