መጽ​ሐፈ ኢዮብ 42

42
1ኢዮ​ብም መለሰ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም እን​ዲህ አለው፦ 2“ሁሉን ታደ​ርግ ዘንድ ቻይ እንደ ሆንህ፥ የሚ​ሳ​ን​ህም እን​ደ​ሌለ ዐወ​ቅሁ። 3ምክ​ርን ከአ​ንተ የሚ​ሰ​ውር፥ ቃሉ​ንም ከአ​ንተ የሚ​ሸ​ል​ግና የሚ​ሸ​ሽግ የሚ​መ​ስ​ለው ማን ነው? የማ​ላ​ስ​ተ​ው​ለ​ው​ንና የማ​ላ​ው​ቀ​ው​ንም ታላ​ቅና ድንቅ ነገር የሚ​ነ​ግ​ረኝ ማን ነው?
4“ጌታ ሆይ፥ እባ​ክህ፥ ስማኝ፥ እኔም ልና​ገር፤ እጠ​ይ​ቅ​ህ​ማ​ለሁ፥ አን​ተም አስ​ተ​ም​ረኝ። 5መስ​ማ​ት​ንስ ስለ አንተ ቀድሞ በጆ​ሮዬ ሰምቼ ነበር፤ አሁን ግን ዐይኔ አየ​ችህ፤ 6ስለ​ዚህ ራሴን እን​ቃ​ለሁ፤ ሰው​ነ​ቴም ቀለጠ። እኔ አፈ​ርና አመድ እንደ ሆንሁ አው​ቃ​ለሁ።”
የኢ​ዮብ ወዳ​ጆች እንደ ተወ​ቀሱ
7እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ይህን ቃል ለኢ​ዮብ ከተ​ና​ገረ በኋላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቴማ​ና​ዊ​ውን ኤል​ፋ​ዝን እን​ዲህ አለው፥ “እንደ ባሪ​ያዬ እንደ ኢዮብ አን​ዲት ቅን ነገ​ርን በፊቴ አል​ተ​ና​ገ​ራ​ች​ሁ​ምና አን​ተና ሁለቱ ባል​ን​ጀ​ሮ​ችህ በድ​ላ​ች​ኋል። 8አሁን እን​ግ​ዲህ ሰባት ወይ​ፈ​ኖ​ች​ንና ሰባት አውራ በጎ​ችን ይዛ​ችሁ ወደ ባሪ​ያዬ ወደ ኢዮብ ዘንድ ሂዱ፥ እር​ሱም የሚ​ቃ​ጠ​ልን መሥ​ዋ​ዕት ስለ ራሳ​ችሁ ያሳ​ር​ግ​ላ​ችሁ። ባሪ​ያ​ዬም ኢዮብ ስለ እና​ንተ ይጸ​ልይ፥ እኔም ፊቱን እቀ​በ​ላ​ለሁ። ስለ እርሱ ባይ​ሆን ባጠ​ፋ​ኋ​ችሁ ነበር። በባ​ሪ​ያዬ በኢ​ዮብ ላይ ቅን ነገ​ርን በፊቴ አል​ተ​ና​ገ​ራ​ች​ሁ​ምና።”
9ቴማ​ና​ዊ​ውም ኤል​ፋዝ፥ አው​ኬ​ና​ዊው በል​ዳ​ዶ​ስና፥ አሜ​ና​ዊው ሶፋር ሄደው እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዳ​ዘ​ዛ​ቸው አደ​ረጉ፤ ስለ ኢዮ​ብም ሲል ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ይቅር አላ​ቸው።
የኢ​ዮብ ጤናና ሀብት እንደ ተመ​ለሰ
10እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኢዮ​ብን አዳ​ነው።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አበ​ለ​ጠ​ገው” ይላል። ኢዮ​ብም ስለ ወዳ​ጆቹ ጸለየ፥ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ኀጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ተወ​ላ​ቸው፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቀድሞ በነ​በ​ረው ገን​ዘቡ ሁሉ ፋንታ ሁለት እጥፍ ከዚ​ያም በላይ አድ​ርጎ ለኢ​ዮብ ሰጠው። 11ወን​ድ​ሞ​ቹና እኅ​ቶቹ ቀድ​ሞም ያው​ቁት የነ​በ​ሩት ሁሉ የሆ​ነ​ውን ሁሉ በሰሙ ጊዜ ወደ እርሱ መጡ፥ በቤ​ቱም ከእ​ርሱ ጋር እን​ጀራ በሉ፥ ጠጡም፤ አጽ​ና​ኑ​ትም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ባመ​ጣ​በት ክፉ ነገር ሁሉ አደ​ነቁ፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ውም ጥማድ በሬ፥#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የበግ ጠቦት” ይላል። አራት ድራ​ህማ የሚ​መ​ዝን ወር​ቅና ብር ሰጡት።
12እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከፊ​ተ​ኛው ይልቅ የኋ​ለ​ኛ​ውን ለኢ​ዮብ ባረከ፤ መን​ጋ​ዎ​ቹም ዐሥራ አራት ሺህ በጎች፥ ስድ​ስት ሺህም ግመ​ሎች፥ አንድ ሺህም ጥማድ በሬ​ዎች፥ አንድ ሺህም እን​ስት አህ​ዮች ነበሩ። 13ደግ​ሞም ሰባት ወን​ዶ​ችና ሦስት ሴቶች ልጆች ተወ​ለ​ዱ​ለት። 14የመ​ጀ​መ​ሪ​ያ​ይ​ቱን ስም ዕለት፥ የሁ​ለ​ተ​ኛ​ይ​ቱ​ንም ስም ቃስያ፥ የሦ​ስ​ተ​ኛ​ይ​ቱ​ንም ስም አማ​ል​ት​ያ​ስ​ቂ​ራስ ብሎ ሰየ​ማ​ቸው። 15ከሰ​ማይ በታች እንደ ኢዮብ ሴቶች ልጆች ያሉ የተ​ዋቡ ሴቶች በሀ​ገሩ ሁሉ አል​ተ​ገ​ኙም፤ አባ​ታ​ቸ​ውም ከወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ቸው ጋር ርስት ሰጣ​ቸው።
16ኢዮ​ብም ከደ​ዌው ከዳነ በኋላ መቶ ሰባ#ዕብ. “መቶ አርባ” ይላል። ዓመት ኖረ፥ ኢዮ​ብም የኖ​ረ​በት ዘመን ሁሉ ሁለት መቶ አርባ#ዕብ. “ሁለት መቶ አርባ ስም​ንት” ይላል። ነው። ልጆ​ቹ​ንና የልጅ ልጆ​ቹ​ንም እስከ አራት ትው​ልድ ድረስ አየ። 17ኢዮ​ብም ሸም​ግሎ ዕድ​ሜም ጠግቦ ሞተ። 18#ምዕ. 42 ከቍ. 18 እስከ 25 በዕብ. የለም። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከሚ​ያ​ነ​ሣ​ቸው ሰዎች ጋር ዳግ​መኛ እን​ደ​ሚ​ነሣ የተ​ጻፈ ነው።
19ይህ ሰው በሶ​ር​ያው መጽ​ሐፍ እን​ደ​ዚህ ተገ​ል​ጦ​አል። የኖ​ረ​በ​ትም ሀገሩ በኤ​ዶ​ም​ያ​ስና በዐ​ረብ አው​ራጃ ያለ አው​ስ​ጢድ ነው። 20ስሙም ቀድሞ ኢዮ​ባብ ነበረ፥ ዐረ​ባ​ዊት ሴት​ንም አገባ። ስሙ ሄኖን የሚ​ባል ልጅ​ንም ወለ​ደ​ች​ለት። እር​ሱም የኤ​ሳው የልጅ ልጅ የዛራ ልጅ ነው። እና​ቱም ባሱ​ራስ ትባል ነበር። 21እር​ሱም ከአ​ብ​ር​ሃም አም​ስ​ተኛ ነው። እር​ሱም በገ​ዛት ሀገር በኤ​ዶ​ም​ያስ የነ​ገሡ ነገ​ሥ​ታት እነ​ዚህ ነበሩ። 22አስ​ቀ​ድሞ የነ​ገሠ የቢ​ዖር ልጅ ባላቅ ነው። የከ​ተ​ማ​ዋም ስም ዲናባ ነበር። 23ከባ​ላ​ቅም በኋላ ስሙ ኢዮብ ይባል የነ​በ​ረው ኢዮ​ባብ ነገሠ። ከእ​ር​ሱም በኋላ በቴ​ማን ሀገር የነ​ገሠ አሶም ነበር። 24ከእ​ር​ሱም በኋላ በሞ​ዓብ ምድረ በዳ የም​ድ​ያ​ምን ሰዎች የገ​ደ​ላ​ቸው የበ​ራድ ልጅ አዳድ ነበር፥ የከ​ተ​ማ​ውም ስም ጌቴም ነበር። 25ወደ እርሱ የመጡ ወዳ​ጆ​ቹም አንዱ ከዔ​ሳው ልጆች የተ​ወ​ለደ በቴ​ማ​ኖን የነ​ገ​ሠው ኤል​ፋዝ፥ በአ​ው​ኪ​ኒ​ዮን የተ​ሾ​መው በል​ዳ​ዶ​ስና የአ​ሜ​ኔ​ዎን ንጉሥ ሶፋር ነበሩ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ