መጽ​ሐፈ ኢዮብ 39

39
1“ዋልያ#ግሪኩ እና ዕብ. “ብሆር” ይላል። የም​ት​ወ​ል​ድ​በ​ትን ጊዜ ታው​ቃ​ለ​ህን?
# ግሪኩ “ዋልያ” የሚል ይጨ​ም​ራል። የም​ታ​ም​ጥ​በ​ት​ንስ ጊዜ ትመ​ለ​ከ​ታ​ለ​ህን?
2እር​ስዋ የም​ት​ወ​ል​ድ​በ​ት​ንስ ሙሉ ወራት ትቈ​ጥ​ራ​ለ​ህን?
ከም​ጥስ ትገ​ላ​ግ​ላ​ታ​ለ​ህን?
3ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንስ ያለ ፍር​ሃት አሳ​ድ​ገ​ሃ​ልን?
መከ​ራ​ቸ​ው​ንስ አስ​ወ​ግ​ደ​ሃ​ልን?
4ልጆ​ቻ​ቸው ያመ​ል​ጣሉ።#ዕብ. “ይጠ​ነ​ክ​ራሉ” ይላል።
ይባ​ዛሉ፥ ይዋ​ለ​ዳ​ሉም።
ይወ​ጣሉ፥ ወደ እነ​ር​ሱም አይ​መ​ለ​ሱም።
5“የሜ​ዳ​ው​ንስ አህያ ነጻ​ነት ማን አወ​ጣው?
ከእ​ስ​ራ​ቱስ ማን ፈታው?
6በረ​ሃ​ውን ለእ​ርሱ ቤት፥
መኖ​ሪ​ያ​ው​ንም በጨው ምድር አድ​ርጌ ሰጠ​ሁት።
7በከ​ተ​ማው ሕዝብ ውካታ ይዘ​ብ​ታል፤
የሚ​ያ​ስ​ፈ​ራ​ው​ንም ጩኸት አይ​ሰ​ማም።
8ተራ​ራ​ውን እንደ መሰ​ም​ሪ​ያው ይመ​ለ​ከ​ተ​ዋል፥
ለም​ለ​ሙ​ንም ሁሉ ይፈ​ል​ጋል።
9“ጎሽ ያገ​ለ​ግ​ልህ ዘንድ ይፈ​ቅ​ዳ​ልን?
ወይስ በግ​ር​ግ​ምህ አጠ​ገብ ያድ​ራ​ልን?
10በቀ​ን​በር ትጠ​ም​ደ​ዋ​ለ​ህን?
በእ​ር​ሻ​ህስ ውስጥ ትልም ያር​ስ​ል​ሃ​ልን?
11ጕል​በ​ቱስ ብርቱ ስለ​ሆነ ትታ​መ​ነ​ዋ​ለ​ህን?
ተግ​ባ​ር​ህ​ንስ ለእ​ርሱ ትተ​ዋ​ለ​ህን?
12ዘር​ህ​ንስ ይመ​ል​ስ​ልህ ዘንድ፥
በአ​ው​ድ​ማ​ህስ ያከ​ማ​ች​ልህ ዘንድ ትታ​መ​ነ​ዋ​ለ​ህን?
13“ሰጎን ክን​ፍ​ዋን በደ​ስታ ታን​ቀ​ሳ​ቅ​ሳ​ለች፥
በፀ​ነ​ሰ​ችም ጊዜ ልት​በላ ትመ​ኛ​ለች፥#በግ​ሪክ ሰባ. ሊ. ይለ​ያል።
14ዕን​ቍ​ላ​ልን በመ​ሬት ላይ ትጥ​ላ​ለች፥
በአ​ፈ​ርም ውስጥ ታሞ​ቀ​ዋ​ለች፥#በግ​እዝ ይለ​ያል።
15እግር ይሰ​ብ​ረው ዘንድ፥
የም​ድረ በዳም አውሬ ይረ​ግ​ጠው ዘንድ ትረ​ሳ​ለች።
16የእ​ር​ስዋ እን​ዳ​ል​ሆኑ በል​ጆ​ችዋ ላይ ትጨ​ክ​ና​ለች፤#በግ​እዝ ይለ​ያል።
ያለ ፍር​ሀ​ትም በከ​ንቱ ትሠ​ራ​ለች፤
17እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጥበ​ብን ከእ​ር​ስዋ ከል​ክ​ሎ​አ​ልና፥#ግእዙ በአ​ወ​ንታ ነው።
ማስ​ተ​ዋ​ል​ንም አል​ሰ​ጣ​ት​ምና።
18በዘ​መ​ንዋ ወደ ላይ ራስ​ዋን ከፍ ከፍ ታደ​ር​ጋ​ለች፥
በፈ​ረ​ሱና በፈ​ረ​ሰ​ኛው ትሣ​ለ​ቃ​ለች።
19“ለፈ​ረስ አንተ ጕል​በ​ቱን ሰጥ​ተ​ኸ​ዋ​ልን?
አን​ገ​ቱ​ንስ ጋማ አል​ብ​ሰ​ኸ​ዋ​ልን?
20በፍ​ጹም የጦር መሣ​ሪያ አስ​ጊ​ጠ​ኸ​ዋ​ልን?
እም​ቢ​ያ​ው​ንስ በብ​ር​ታት የከ​በረ አድ​ር​ገ​ኸ​ዋ​ልን?
21በኮ​ቴው በሸ​ለ​ቆው ውስጥ ይጐ​ደ​ፍ​ራል፥
በጕ​ል​በ​ቱም ወደ ሜዳ ይወ​ጣል።
22በሚ​ገ​ና​ኘው ፍላጻ ላይ ይስ​ቃል።
ከሰ​ይ​ፍም ፊት አይ​መ​ለ​ስም።
23ቀስ​ትና ጦር በእ​ርሱ ላይ ይበ​ረ​ታሉ፥
24በቍ​ጣ​ውም መሬ​ትን ያጠ​ፋል፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. እና ዕብ. “ይወ​ጣል” ይላል።
የመ​ለ​ከ​ትም ድምፅ እስ​ከ​ሚ​ሰ​ማው አያ​ም​ንም።
25የመ​ለ​ከ​ትም ድምፅ ሲሰማ፦ እሰይ ይላል፤
ከሩ​ቅም ሆኖ ሰል​ፍ​ንና የአ​ለ​ቆ​ችን ጩኸት፥
የሠ​ራ​ዊ​ቱ​ንም ውካታ ያሸ​ታል።
26“በውኑ ከጥ​በ​ብህ የተ​ነሣ ጭል​ፊት ያን​ዣ​ብ​ባ​ልን?
ወይስ ክን​ፎ​ቹን ወደ ደቡብ ይዘ​ረ​ጋ​ልን?
27በአ​ፍህ ትእ​ዛዝ ንስር ከፍ ከፍ ይላ​ልን?
ጆፌ አሞ​ራስ ልጆ​ቹን አቅፎ ያድ​ራ​ልን?
28በዓ​ለቱ ገደል ላይ ይኖ​ራል፤
በገ​ደሉ ገመ​ገ​ምና በጥጉ ያድ​ራል።
29በዚ​ያም ሆኖ የሚ​በ​ላ​ውን ይፈ​ል​ጋል፤
ዐይ​ኖ​ቹም በሩቁ ይመ​ለ​ከ​ታሉ።
30ጫጭ​ቶ​ቹም ወደ ደም ይሮ​ጣሉ፥
በድን ወደ አለ​በ​ትም ስፍራ ወዲ​ያ​ውኑ ይደ​ር​ሳሉ።”

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ