ኦሪት ዘፍ​ጥ​ረት 49

49
ያዕ​ቆብ ልጆ​ቹን እንደ መረ​ቃ​ቸው
1ያዕ​ቆ​ብም ልጆ​ቹን ጠርቶ እን​ዲህ አላ​ቸው፥ “በኋ​ለ​ኛው ዘመን የሚ​ያ​ገ​ኛ​ች​ሁን እን​ድ​ነ​ግ​ራ​ችሁ ተሰ​ብ​ሰቡ። 2እና​ንት የያ​ዕ​ቆብ ልጆች ኑ፥ ተሰ​ብ​ሰቡ፤ ስሙም፤ አባ​ታ​ችሁ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም አድ​ምጡ።
3“ሮቤል እርሱ የበ​ኵር ልጄና ኀይሌ፥ የል​ጆ​ችም#ዕብ. “የጕ​ብ​ዝ​ናዬ” ይላል። መጀ​መ​ሪያ ነው፤ ክፉ ሆነ፤ አን​ገ​ቱ​ንም አደ​ነ​ደነ።#ዕብ. “የክ​ብር አለ​ቃና የኀ​ይል አለቃ” ይላል። ጭንቅ ነገ​ር​ንም አደ​ረገ። 4እንደ ውኃ የሚ​ዋ​ልል ነው፤ ኀይል የለ​ውም፤#ዕብ. “አለ​ቅ​ነት ለአ​ንተ አይ​ሁን” ይላል። ወደ አባቱ መኝታ ወጥ​ቶ​አ​ልና፤ ያን ጊዜ የወ​ጣ​በ​ትን አልጋ አር​ክ​ሶ​አ​ልና።
5“ስም​ዖ​ንና ሌዊ ወን​ድ​ማ​ማ​ቾች ናቸው፤ በጭ​ቅ​ጭ​ቃ​ቸ​ውና በጦ​ራ​ቸው ዐመ​ፅን ፈጸ​ሙ​አት። 6በም​ክ​ራ​ቸው ሰው​ነቴ አት​ገ​ና​ኛ​ቸው፤ ዐሳ​ቤም በአ​መ​ፃ​ቸው አት​ተ​ባ​በ​ርም፤ በቍ​ጣ​ቸው ሰውን ገድ​ለ​ዋ​ልና፤ በገዛ ፈቃ​ዳ​ቸ​ውም የሀ​ገ​ርን ሥር ቈር​ጠ​ዋ​ልና። 7ቍጣ​ቸው ርጉም ይሁን፤ ጽኑ ነበ​ርና፤ ኵር​ፍ​ታ​ቸ​ውም ብርቱ ነበ​ርና፤ በያ​ዕ​ቆብ እከ​ፋ​ፍ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም እበ​ታ​ት​ና​ቸ​ዋ​ለሁ።
8“ይሁዳ፥ ወን​ድ​ሞ​ችህ አን​ተን ያመ​ሰ​ግ​ኑ​ሃል፤ እጅህ በጠ​ላ​ቶ​ችህ ደን​ደስ ላይ ነው፤ የአ​ባ​ትህ ልጆች በፊ​ትህ ይሰ​ግ​ዳሉ። 9ይሁዳ የአ​ን​በሳ ደቦል ነው፤ ልጄ ሆይ፥ ከመ​ሰ​ማ​ሪ​ያህ ወጣህ፤ እንደ አን​በሳ ተኛህ፤ አን​ቀ​ላ​ፋ​ህም፤ እንደ አን​በ​ሳም ደቦል የሚ​ቀ​ሰ​ቅ​ስህ የለም። 10መን​ግ​ሥት ከይ​ሁዳ አይ​ጠ​ፋም፤ ምስ​ፍ​ናም ከአ​ብ​ራኩ፥ ለእ​ርሱ የሚ​ጠ​ብ​ቀ​ውን እስ​ኪ​ያ​ገኝ ድረስ፤ የአ​ሕ​ዛብ ተስ​ፋ​ቸው እርሱ ነውና፤ 11አህ​ያ​ይ​ቱን በወ​ይን ግንድ ያስ​ራል፤ የአ​ህ​ያ​ይ​ቱ​ንም ግል​ገል በወ​ይን ሐረግ፤ ልብ​ሱን በወ​ይን ያጥ​ባል፤ መጐ​ና​ጸ​ፊ​ያ​ው​ንም በዘ​ለ​ላው ደም። 12ዐይ​ኖቹ ከወ​ይን ይልቅ ደስ ያሰ​ኛሉ፤ ጥር​ሱም ከወ​ተት ይልቅ ነጭ ነው።
13“ዛብ​ሎን ጫማ​ውን አዝቦ ይኖ​ራል፤ እር​ሱም እንደ መር​ከ​ቦች ወደብ ይሆ​ናል፤ ዳር​ቻ​ውም እስከ ሲዶና ይሰ​ፋል።
14“ይሳ​ኮር መል​ካም ነገ​ርን ወደደ፤ በተ​ወ​ራ​ራ​ሾ​ቹም መካ​ከል ያር​ፋል። 15ዕረ​ፍ​ትም መል​ካም መሆ​ን​ዋን፥ ምድ​ሪ​ቱም የለ​ማች መሆ​ን​ዋን በአየ ጊዜ ምድ​ርን ያር​ሳት ዘንድ ትከ​ሻ​ውን ዝቅ አደ​ረገ፤ በሥ​ራም ገበሬ ሆነ።
16“ዳን ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ እንደ አንዱ በወ​ገኑ ይፈ​ር​ዳል፤ 17ዳን በጎ​ዳና ላይ እን​ደ​ሚ​ያ​ደባ እባብ ይሆ​ናል፤ በመ​ን​ገ​ዱም የፈ​ረ​ሱን ሰኰና እን​ደ​ሚ​ና​ደፍ እንደ ቀን​ዳም እባብ ነው፤ ፈረ​ሰ​ኛ​ውም ወደ​ኋ​ላው ይወ​ድ​ቃል። 18እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ያድ​ነው ዘንድ ይጠ​ብ​ቃል።#ዕብ. “እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ መድ​ኀ​ኒ​ት​ህን እጠ​ብ​ቃ​ለሁ” ይላል።
19“ጋድን ሽፍ​ቶች ቀሙት፤ እር​ሱም ፍለ​ጋ​ቸ​ውን ተከ​ታ​ትሎ ቀማ​ቸው።
20“የአ​ሴር እን​ጀራ ወፍ​ራም ነው፤ እር​ሱም ለአ​ለ​ቆች ደስ የሚ​ያ​ሰኝ መብ​ልን ይሰ​ጣል።
21“ንፍ​ታ​ሌም በፍ​ሬው ላይ ውበ​ትን የሚ​ሰጥ ሰፊ ዘን​ባባ ነው።#ዕብ. “የተ​ፈታ ሚዳቋ ነው መል​ካም ቃልን ይሰ​ጣል” ይላል።
22“ዮሴፍ የሚ​ያ​ድግ ልጅ ነው፤ ለእኔ በጣም የተ​ወ​ደደ የሚ​ቀ​ና​ል​ኝና የሚ​ያ​ድ​ግ​ልኝ ልጅ ነው፤ ወደ እኔ የሚ​መ​ለ​ስም ጐል​ማሳ ነው።#ዕብ. “ዮሴፍ ትንሹ የፍሬ ዛፍ ነው ፤ በም​ንጭ አጠ​ገብ የሚ​ያ​ፈራ የፍሬ ዛፍ ነው ፤ ሐረ​ጎቹ በቅ​ጥር ላይ ያድ​ጋሉ” ይላል። 23በም​ክ​ራ​ቸው የሰ​ደ​ቡት ጌቶች ሆኑ​በት፤ ቀስ​ተ​ኞ​ችም ወጉት፤ 24ነገር ግን ቀስ​ቶ​ቻ​ቸው በኀ​ይል ተቀ​ጠ​ቀጡ፤ የእ​ጆ​ቻ​ቸው ክንድ ሥርም በያ​ዕ​ቆብ ኀያል እጅ ዛለ፤ በዚ​ያም በአ​ባ​ትህ አም​ላክ ዘንድ እስ​ራ​ኤ​ልን አጸ​ናው።
25“የእኔ አም​ላክ ረዳህ፤ ከላይ በሰ​ማይ በረ​ከት፥ ሁሉ በሚ​ገ​ኝ​ባት፥ በም​ድር በረ​ከት፥ በጡ​ትና በማ​ኅ​ፀን በረ​ከት ባረ​ከህ፤ 26የአ​ባ​ት​ህና የእ​ና​ትህ በረ​ከ​ቶች ጽኑ​ዓን ከሆኑ ከተ​ራ​ሮች በረ​ከ​ቶች ይልቅ ይበ​ል​ጣሉ፤ ዘለ​ዓ​ለ​ማ​ው​ያን ከሆኑ ከኮ​ረ​ብ​ቶ​ችም#ግእዝ “በረ​ከተ መላ​እ​ክ​ቲሁ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር” ይላል። በረ​ከ​ቶች ይልቅ ኀያ​ላን ናቸው፤ እነ​ር​ሱም በዮ​ሴፍ ራስ ላይ ይሆ​ናሉ፤ በወ​ን​ድ​ሞቹ መካ​ከል አለቃ በሆ​ነ​ውም ራስ አናት ላይ ይሆ​ናሉ።
27“ብን​ያም ነጣቂ ተኵላ ነው፤ በጥ​ዋት ይበ​ላል፤ የማ​ረ​ከ​ው​ንም ምግ​ቡን በማታ ለሕ​ዝብ ይሰ​ጣል።” 28እነ​ዚ​ህም ሁሉ ዐሥራ ሁለቱ የያ​ዕ​ቆብ ልጆች ናቸው፤ አባ​ታ​ቸ​ውም ይህን ነገር ነገ​ራ​ቸው፤ ባረ​ካ​ቸ​ውም፤ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸ​ው​ንም እንደ በረ​ከ​ታ​ቸው ባረ​ካ​ቸው።
የያ​ዕ​ቆብ መሞ​ትና መቀ​በር
29እን​ዲ​ህም ብሎ አዘ​ዛ​ቸው፥ “እኔ ወደ ወገ​ኖች እሰ​በ​ሰ​ባ​ለሁ፤ በኬ​ጢ​ያ​ዊው በኤ​ፍ​ሮን እርሻ ላይ ባለ​ችው ዋሻ ከአ​ባ​ቶች ጋር ቅበ​ሩኝ፤ እር​ስ​ዋም በከ​ነ​ዓን ምድር በመ​ምሬ ፊት ያለች፥ 30አብ​ር​ሃም ለመ​ቃ​ብር ርስት ከኬ​ጢ​ያ​ዊው ከኤ​ፍ​ሮን ከእ​ር​ሻው ጋር የገ​ዛት፥ ባለ ድርብ ክፍል ዋሻ ናት። 31አብ​ር​ሃ​ም​ንና ሚስቱ ሣራ​ንም በዚያ ቀበ​ሩ​አ​ቸው፤ ይስ​ሐ​ቅ​ንና ሚስቱ ርብ​ቃ​ንም በዚያ ቀበ​ሩ​አ​ቸው፤ ከዚ​ያም እኔ ልያን ቀበ​ር​ኋት 32እር​ሻ​ውና በእ​ር​ስዋ ላይ ያለ​ችው ዋሻ ከኬጢ ልጆች የተ​ገዙ ናቸው።” 33ያዕ​ቆ​ብም ትእ​ዛ​ዙን ለል​ጆቹ ተና​ግሮ በፈ​ጸመ ጊዜ እግ​ሮ​ቹን በአ​ል​ጋው ላይ ዘር​ግቶ ሞተ፤ ወደ ወገ​ኖ​ቹም ተጨ​መረ።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ