መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 32:24-33

መጽ​ሐፈ ዜና መዋ​ዕል ካልእ 32:24-33 አማ2000

በዚ​ያም ወራት ሕዝ​ቅ​ያስ እስከ ሞት ድረስ ታመመ፤ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ጸለየ፤ እር​ሱም ሰማው፤ ምል​ክ​ትም ሰጠው። ሕዝ​ቅ​ያስ ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሰጠው ቸር​ነት መጠን አላ​ደ​ረ​ገም፤ ልቡም ኮራ፤ ስለ​ዚ​ህም በእ​ር​ሱና በይ​ሁዳ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ላይ ቍጣ ሆነ። ሕዝ​ቅ​ያ​ስም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ከሚ​ኖሩ ሰዎች ጋር ስለ ልቡ ኵራት ሰው​ነ​ቱን አዋ​ረደ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በሕ​ዝ​ቅ​ያስ ዘመን ቍጣ​ውን አላ​መ​ጣ​ባ​ቸ​ውም። ለሕ​ዝ​ቅ​ያ​ስም እጅግ ብዙ ሀብ​ትና ክብር ነበ​ረው፤ ለብ​ርና ለወ​ር​ቅም፥ ለከ​በ​ረው ዕን​ቍና ለሽ​ቱው፥ ለጋ​ሻ​ውና ውድ ለሆ​ነው ዕቃ ሁሉ ግምጃ ቤቶ​ችን ሠራ። ለእ​ህ​ልና ለወ​ይን ጠጅም ለዘ​ይ​ትም ዕቃ ቤቶች፥ ለልዩ ልዩም እን​ስሳ ጋጥ፥ ለመ​ን​ጎ​ችም በረት ሠራ። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እጅግ ብዙ ጥሪት ሰጥ​ቶት ነበ​ርና ከተ​ሞ​ችን ለራሱ ሠራ፤ ብዙም የበ​ግና የላም መንጋ ሰበ​ሰበ። ይህም ሕዝ​ቅ​ያስ የላ​ይ​ኛ​ውን የግ​ዮ​ንን ውኃ ምንጭ ደፈነ፤ በዳ​ዊ​ትም ከተማ በም​ዕ​ራብ በኩል አቅ​ንቶ አወ​ረ​ደው። ሕዝ​ቅ​ያ​ስም በሥ​ራው ሁሉ ተከ​ና​ወነ። ነገር ግን የባ​ቢ​ሎን መሳ​ፍ​ንት መል​እ​ክ​ተ​ኞች በሀ​ገሩ ላይ ስለ ተደ​ረ​ገው ተአ​ም​ራት ይጠ​ይ​ቁት ዘንድ ወደ እርሱ በተ​ላኩ ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይፈ​ት​ነ​ውና በልቡ ያለ​ውን ሁሉ ያውቅ ዘንድ ተወው። የሕ​ዝ​ቅ​ያ​ስም የቀ​ሩት ነገ​ሮች፥ ቸር​ነ​ቱም፥ እነሆ፥ በአ​ሞጽ ልጅ በነ​ቢዩ በኢ​ሳ​ይ​ያስ ራእይ በይ​ሁ​ዳና በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ነገ​ሥ​ታት መጽ​ሐፍ ተጽ​ፈ​ዋል። ሕዝ​ቅ​ያ​ስም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፤ በዳ​ዊ​ትም ልጆች መቃ​ብር በላ​ይ​ኛው ክፍል ቀበ​ሩት፤ በይ​ሁ​ዳና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖ​ሩ​ትም ሁሉ በሞቱ አከ​በ​ሩት። ልጁም ምናሴ በእ​ርሱ ፋንታ ነገሠ።