2ኛ የዮሐንስ መልእክት መግቢያ

መግቢያ
ሁለተኛው የዮሐንስ መልእክት የተጻፈው በሽማግሌው ሐዋርያ በዮሐንስ ሲሆን የተጻፈውም ለተመረጠችው እመቤትና ለልጆችዋ ነው። በእመቤት የተመሰለችው የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ስትሆን፥ ልጆችዋ ደግሞ የአባሎችዋ ምሳሌዎች ናቸው፤ ይህ አጭር መልእክት የተጻፈው ምእመናን እርስ በርስ እንዲዋደዱ ለማሳሰብና ከሐሰተኛ ትምህርት እንዲርቁ ለማስጠንቀቅ ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
መቅድም (1-3)
ፍቅር ከሁሉ በላይ ነው (4-6)
ስለ ሐሰተኛ ትምህርት ማስጠንቀቂያ (7-11)
ማጠቃለያ (12-13)
ምዕራፍ

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ